
ቡታጅራ፤ የካቲት 18/2017 (ኢዜአ) :- የግብርና ምርምር ተቋማት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተሻሻሉ ዝርያዎችን በስፋት ተደራሽ ሊያደርጉ እንደሚገባ ተገለጸ።
የክልሉ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዓመታዊ የምርምር ሥራዎች በተመለከተ በቡታጅራ ከተማ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ሱሩር ፤ በግብርናው ዘርፍ የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።
የግብርና ምርምር ተቋማት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የእንስሳትና የሰብል ዝርያዎችን በስፋት ተደራሽ በማድረግ የላቀ ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
የክልሉ የግብርና ምርምር ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር ፀጋዬ ተረፈ፤ የግብርናውን ዘርፍ የሚያግዙ በርካታ የምርምር ስራዎች እየተሰሩ ተደራሽም እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

የግብርና ምርምር ተቋማቱ በተለይም በሰብልና የእንስስት ዝርያ ማሻሻል ላይ አተኩረው እየሰሩ መሆኑንም አስረድተዋል።
ለአብነትም በሽታና ድርቅን መቋቋም የሚችሉና ምርታማ የሆኑ በስንዴ ሰባት እንዲሁም በባቄላ ሶስት ዝርያዎች በማፍለቅ የተሰበሰበ ከ3 ሺህ 200 ኩንታል በላይ የቅድመ መስራችና መስራች ዝርያዎች መሰራጨቱን ተናግረዋል።
በእንስሳት ልማትም የተሻሻሉ የወተትና ስጋ ከብቶች እርባታ ላይ ውጤታማ የምርምር ስራዎች ተከናውነው ለአርሶ አደሮች ተደራሽ እየተደረጉ ነው ብለዋል።
ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው መድረክ 49 ያለቁና 109 በሂደት ላይ ያሉ እንዲሁም 302 አዳዲስ የምርምር ውጤቶች እንደሚቀርቡም ይጠበቃል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025