የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>የግብርና ምርምር ተቋማት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተሻሻሉ ዝርያዎችን በስፋት ተደራሽ ሊያደርጉ ይገባል</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

ቡታጅራ፤ የካቲት 18/2017 (ኢዜአ) :- የግብርና ምርምር ተቋማት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተሻሻሉ ዝርያዎችን በስፋት ተደራሽ ሊያደርጉ እንደሚገባ ተገለጸ።

የክልሉ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዓመታዊ የምርምር ሥራዎች በተመለከተ በቡታጅራ ከተማ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።


በመድረኩ ላይ የተገኙት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ሱሩር ፤ በግብርናው ዘርፍ የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።

የግብርና ምርምር ተቋማት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የእንስሳትና የሰብል ዝርያዎችን በስፋት ተደራሽ በማድረግ የላቀ ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

የክልሉ የግብርና ምርምር ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር ፀጋዬ ተረፈ፤ የግብርናውን ዘርፍ የሚያግዙ በርካታ የምርምር ስራዎች እየተሰሩ ተደራሽም እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።


የግብርና ምርምር ተቋማቱ በተለይም በሰብልና የእንስስት ዝርያ ማሻሻል ላይ አተኩረው እየሰሩ መሆኑንም አስረድተዋል።

ለአብነትም በሽታና ድርቅን መቋቋም የሚችሉና ምርታማ የሆኑ በስንዴ ሰባት እንዲሁም በባቄላ ሶስት ዝርያዎች በማፍለቅ የተሰበሰበ ከ3 ሺህ 200 ኩንታል በላይ የቅድመ መስራችና መስራች ዝርያዎች መሰራጨቱን ተናግረዋል።

በእንስሳት ልማትም የተሻሻሉ የወተትና ስጋ ከብቶች እርባታ ላይ ውጤታማ የምርምር ስራዎች ተከናውነው ለአርሶ አደሮች ተደራሽ እየተደረጉ ነው ብለዋል።

ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው መድረክ 49 ያለቁና 109 በሂደት ላይ ያሉ እንዲሁም 302 አዳዲስ የምርምር ውጤቶች እንደሚቀርቡም ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026