
አዲስ አበባ፤የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማቀላጠፍ ሀገራት በትብብር ወደ ተግባር መግባት እንዳለባቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 'ኤክስቴንሲያ' ከተሰኘ ሁነት አመቻች ጋር ያዘጋጀው የተቀላጠፈ የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባ "አዳዲስ ዕድሎችን መጠቀም" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ የተቀላጠፈ የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባ የአፍሪካን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የወደፊት እጣ ፋንታ የሚወስን ነው።
መርሐ ግብሩ የፓን አፍሪካ ፖሊሲ አውጪዎች፣ተቆጣጣሪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች እና ባለሀብቶች የአፍሪካን የዲጂታል ሽግግር ለማቀላጠፍ ተሰባስበው የሚመክሩበት መሆኑን ገልጸዋል።
የዲጂታል ቴክኖሎጂ የአፍሪካን ኢኮኖሚ መልክ የሚቀይር፣ የአዲስ የሥራ ዕድሎችን የሚፈጥር እና አፍሪካ በዓለም ገበያ ላይ ያላትን ድርሻ የሚወስን መሆኑንም ጠቁመዋል።
የዲጂታል አገልግሎት፣ቀጣይነት ያለው ኢኮኖሚ ለመገንባት አይ ሲ ቲን መሰረት ያደረጉ ኢንዱስትሪዎች ማስፋፋት እና አካታች እድገት ለማስመዝገብ ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።
በመሆኑም የዲጂታል ሽግግርን እውን ለማድረግ ከንግግር ያለፈ የተግባር አንድነት፣ትብብር እና ቆራጥ እርምጃ ያስፈልጋል ብለዋል።
የአፍሪካ ትልቁ ጸጋ ጥሬ እቃ ብቻ አይደለም ያሉት ሚኒስትሩ፤ ሩቅ አሳቢ መሪዎች፣ የብሩህ አዕምሮ ባለቤቶች፣ስራ ፈጣሪዎች ጭምር መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በመሆኑም በሁሉም ማዕዘናት በጋራ በመስራት አፍሪካን መቀበል ብቻ ሳይሆን መሪ የምናደርግበትን እድል በአፋጣኝ መጠቀም ይገባናል ብለዋል።
የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባን በተባባሪነት ያዘጋጀው የኤክስቴንሲያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ታሪቅ ማሊክ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በሳይንስና ቴክኖሎጂ እመርታዊ እድገት አስመዝግባለች ብለዋል፡፡
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂ ገቢራዊ በማድረግ በማህበራዊ ፤ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስኮች ተጨባጭ ውጤት ማምጣቷንም ገልጸዋል፡፡
መንግስት የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችን በማዘመኑ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ማደጉን ገልጸው፥ ይህም ለዲጂታል ሽግግር ያለውን ቁርጠኝነት ማሳያዎች መሆናቸውን አንስተዋል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽ

ሩን ዓለማየሁ (ዶ/ር)፥የተቀላጠፈ የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባ የአፍሪካን ዲጂታል ስትራቴጂን ለማሳካት አጋዥ ሁነት ነው ብለዋል፡፡
መድረኩ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ልምድ የምታካፍልበት ከሌሎች ሀገሮች የምትማርበት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026