አዲስ አበባ፤የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማቀላጠፍ ሀገራት በትብብር ወደ ተግባር መግባት እንዳለባቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 'ኤክስቴንሲያ' ከተሰኘ ሁነት አመቻች ጋር ያዘጋጀው የተቀላጠፈ የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባ "አዳዲስ ዕድሎችን መጠቀም" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ የተቀላጠፈ የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባ የአፍሪካን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የወደፊት እጣ ፋንታ የሚወስን ነው።
መርሐ ግብሩ የፓን አፍሪካ ፖሊሲ አውጪዎች፣ተቆጣጣሪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች እና ባለሀብቶች የአፍሪካን የዲጂታል ሽግግር ለማቀላጠፍ ተሰባስበው የሚመክሩበት መሆኑን ገልጸዋል።
የዲጂታል ቴክኖሎጂ የአፍሪካን ኢኮኖሚ መልክ የሚቀይር፣ የአዲስ የሥራ ዕድሎችን የሚፈጥር እና አፍሪካ በዓለም ገበያ ላይ ያላትን ድርሻ የሚወስን መሆኑንም ጠቁመዋል።
የዲጂታል አገልግሎት፣ቀጣይነት ያለው ኢኮኖሚ ለመገንባት አይ ሲ ቲን መሰረት ያደረጉ ኢንዱስትሪዎች ማስፋፋት እና አካታች እድገት ለማስመዝገብ ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።
በመሆኑም የዲጂታል ሽግግርን እውን ለማድረግ ከንግግር ያለፈ የተግባር አንድነት፣ትብብር እና ቆራጥ እርምጃ ያስፈልጋል ብለዋል።
የአፍሪካ ትልቁ ጸጋ ጥሬ እቃ ብቻ አይደለም ያሉት ሚኒስትሩ፤ ሩቅ አሳቢ መሪዎች፣ የብሩህ አዕምሮ ባለቤቶች፣ስራ ፈጣሪዎች ጭምር መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በመሆኑም በሁሉም ማዕዘናት በጋራ በመስራት አፍሪካን መቀበል ብቻ ሳይሆን መሪ የምናደርግበትን እድል በአፋጣኝ መጠቀም ይገባናል ብለዋል።
የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባን በተባባሪነት ያዘጋጀው የኤክስቴንሲያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ታሪቅ ማሊክ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በሳይንስና ቴክኖሎጂ እመርታዊ እድገት አስመዝግባለች ብለዋል፡፡
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂ ገቢራዊ በማድረግ በማህበራዊ ፤ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስኮች ተጨባጭ ውጤት ማምጣቷንም ገልጸዋል፡፡
መንግስት የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችን በማዘመኑ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ማደጉን ገልጸው፥ ይህም ለዲጂታል ሽግግር ያለውን ቁርጠኝነት ማሳያዎች መሆናቸውን አንስተዋል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽ
ሩን ዓለማየሁ (ዶ/ር)፥የተቀላጠፈ የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባ የአፍሪካን ዲጂታል ስትራቴጂን ለማሳካት አጋዥ ሁነት ነው ብለዋል፡፡
መድረኩ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ልምድ የምታካፍልበት ከሌሎች ሀገሮች የምትማርበት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025