
አዲስ አበባ፤የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማቀላጠፍ ሀገራት በትብብር ወደ ተግባር መግባት እንዳለባቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 'ኤክስቴንሲያ' ከተሰኘ ሁነት አመቻች ጋር ያዘጋጀው የተቀላጠፈ የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባ "አዳዲስ ዕድሎችን መጠቀም" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት፣ የተቀላጠፈ የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባ የአፍሪካን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የወደፊት እጣ ፋንታ የሚወስን ነው።
መርሐ ግብሩ የፓን አፍሪካ ፖሊሲ አውጪዎች፣ተቆጣጣሪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች እና ባለሀብቶች የአፍሪካን የዲጂታል ሽግግር ለማቀላጠፍ ተሰባስበው የሚመክሩበት መሆኑን ገልጸዋል።
የዲጂታል ቴክኖሎጂ የአፍሪካን ኢኮኖሚ መልክ የሚቀይር፣ የአዲስ የሥራ ዕድሎችን የሚፈጥር እና አፍሪካ በዓለም ገበያ ላይ ያላትን ድርሻ የሚወስን መሆኑንም ጠቁመዋል።
የዲጂታል አገልግሎት፣ቀጣይነት ያለው ኢኮኖሚ ለመገንባት አይ ሲ ቲን መሰረት ያደረጉ ኢንዱስትሪዎች ማስፋፋት እና አካታች እድገት ለማስመዝገብ ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።
በመሆኑም የዲጂታል ሽግግርን እውን ለማድረግ ከንግግር ያለፈ የተግባር አንድነት፣ትብብር እና ቆራጥ እርምጃ ያስፈልጋል ብለዋል።
የአፍሪካ ትልቁ ጸጋ ጥሬ እቃ ብቻ አይደለም ያሉት ሚኒስትሩ፤ ሩቅ አሳቢ መሪዎች፣ የብሩህ አዕምሮ ባለቤቶች፣ስራ ፈጣሪዎች ጭምር መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በመሆኑም በሁሉም ማዕዘናት በጋራ በመስራት አፍሪካን መቀበል ብቻ ሳይሆን መሪ የምናደርግበትን እድል በአፋጣኝ መጠቀም ይገባናል ብለዋል።
የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባን በተባባሪነት ያዘጋጀው የኤክስቴንሲያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ታሪቅ ማሊክ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በሳይንስና ቴክኖሎጂ እመርታዊ እድገት አስመዝግባለች ብለዋል፡፡
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂ ገቢራዊ በማድረግ በማህበራዊ ፤ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስኮች ተጨባጭ ውጤት ማምጣቷንም ገልጸዋል፡፡
መንግስት የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችን በማዘመኑ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ማደጉን ገልጸው፥ ይህም ለዲጂታል ሽግግር ያለውን ቁርጠኝነት ማሳያዎች መሆናቸውን አንስተዋል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽ

ሩን ዓለማየሁ (ዶ/ር)፥የተቀላጠፈ የዲጂታል ሽግግር 2025 ስብሰባ የአፍሪካን ዲጂታል ስትራቴጂን ለማሳካት አጋዥ ሁነት ነው ብለዋል፡፡
መድረኩ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ልምድ የምታካፍልበት ከሌሎች ሀገሮች የምትማርበት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025