የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማትን አገልግሎት ማዘመንና ተደራሽነት ማስፋት ይገባል</p>

Feb 27, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ የካቲት 19/2017 (ኢዜአ)፦ በክልሉ የአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ማዘመንና ተደራሽነትን ማስፋት እንደሚገባ የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ገለፁ።

የጋምቤላ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም በነባርና በአዳዲስ የስራ መመሪያዎች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዐውደ ጥናት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ እየተካሄደ ነው።


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የጋምቤላ ክልል አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም ቦርድ ሰብሳቢ ጋትሉክ ሮን (ዶ/ር) እንዳሉት አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማትን አገልግሎት ማዘመንና ተደራሽነት ማስፋት ይገባል

የብድርና ቁጠባ ተቋም አገልግሎትን በማሻሻል የስራ አጥ ዜጎችን ተጠቃሚነት ለማስፋት እየተከናወነ ያለውን ስራ ማጠናከር ይገባልም ብለዋል።

ተቋሙ ለተገልጋዮች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ተቋማዊ አደረጃጀቱን ማሻሻልና ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ታግዞ መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል።

በተለይም የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን የዜጎችን የብድርና ቁጠባ ፍላጎት ለማርካት ነባርና አዳዲስ መመሪያዎችን ተግባራዊ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት መጠናከር ያለበት ነው ብለዋል።

ተቋሙ የዜጎችን የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ ብድር በመስጠት ወጣቶችን ከስራ ጠባቂነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።

የጋምቤላ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም ኃላፊ አቶ ኡቻን ኡቻን በበኩላቸው የክልሉ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም የፋይናንስ አካታችነትን በመከተል ስራ አጥ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል።

በተለይም ተቋሙ የገንዘብ አቅሙን በማጠናከር ዘላቂ፣ ተደራሽና ፈጣን የሆነ አገልግሎት ለመስጠት አዳዲስ የአሰራር ስርዓቶችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የዛሬው ዐውደ ጥናት ዓላማም ባለድርሻ አካላት በተቋሙ አዳዲስ መመሪያዎች ዙሪያ በቂ ግንዛቤ በመያዝ የአጋርነታቸውን ሚና እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።

በዐውደ ጥናቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የተቋሙ የቦርድ አባላት፣ የዞንና የወረዳ የዘርፉ አመራሮችና አጋር አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025