
ጋምቤላ፤ የካቲት 19/2017 (ኢዜአ)፦ በክልሉ የአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ማዘመንና ተደራሽነትን ማስፋት እንደሚገባ የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ገለፁ።
የጋምቤላ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም በነባርና በአዳዲስ የስራ መመሪያዎች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዐውደ ጥናት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የጋምቤላ ክልል አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም ቦርድ ሰብሳቢ ጋትሉክ ሮን (ዶ/ር) እንዳሉት አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማትን አገልግሎት ማዘመንና ተደራሽነት ማስፋት ይገባል
የብድርና ቁጠባ ተቋም አገልግሎትን በማሻሻል የስራ አጥ ዜጎችን ተጠቃሚነት ለማስፋት እየተከናወነ ያለውን ስራ ማጠናከር ይገባልም ብለዋል።
ተቋሙ ለተገልጋዮች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ተቋማዊ አደረጃጀቱን ማሻሻልና ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ታግዞ መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል።
በተለይም የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን የዜጎችን የብድርና ቁጠባ ፍላጎት ለማርካት ነባርና አዳዲስ መመሪያዎችን ተግባራዊ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት መጠናከር ያለበት ነው ብለዋል።
ተቋሙ የዜጎችን የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ ብድር በመስጠት ወጣቶችን ከስራ ጠባቂነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
የጋምቤላ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም ኃላፊ አቶ ኡቻን ኡቻን በበኩላቸው የክልሉ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም የፋይናንስ አካታችነትን በመከተል ስራ አጥ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል።
በተለይም ተቋሙ የገንዘብ አቅሙን በማጠናከር ዘላቂ፣ ተደራሽና ፈጣን የሆነ አገልግሎት ለመስጠት አዳዲስ የአሰራር ስርዓቶችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የዛሬው ዐውደ ጥናት ዓላማም ባለድርሻ አካላት በተቋሙ አዳዲስ መመሪያዎች ዙሪያ በቂ ግንዛቤ በመያዝ የአጋርነታቸውን ሚና እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።
በዐውደ ጥናቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የተቋሙ የቦርድ አባላት፣ የዞንና የወረዳ የዘርፉ አመራሮችና አጋር አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025