
ጋምቤላ፤ የካቲት 19/2017 (ኢዜአ)፦ በክልሉ የአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ማዘመንና ተደራሽነትን ማስፋት እንደሚገባ የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) ገለፁ።
የጋምቤላ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም በነባርና በአዳዲስ የስራ መመሪያዎች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዐውደ ጥናት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የጋምቤላ ክልል አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም ቦርድ ሰብሳቢ ጋትሉክ ሮን (ዶ/ር) እንዳሉት አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማትን አገልግሎት ማዘመንና ተደራሽነት ማስፋት ይገባል
የብድርና ቁጠባ ተቋም አገልግሎትን በማሻሻል የስራ አጥ ዜጎችን ተጠቃሚነት ለማስፋት እየተከናወነ ያለውን ስራ ማጠናከር ይገባልም ብለዋል።
ተቋሙ ለተገልጋዮች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ተቋማዊ አደረጃጀቱን ማሻሻልና ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ ታግዞ መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል።
በተለይም የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን የዜጎችን የብድርና ቁጠባ ፍላጎት ለማርካት ነባርና አዳዲስ መመሪያዎችን ተግባራዊ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት መጠናከር ያለበት ነው ብለዋል።
ተቋሙ የዜጎችን የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ ብድር በመስጠት ወጣቶችን ከስራ ጠባቂነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
የጋምቤላ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም ኃላፊ አቶ ኡቻን ኡቻን በበኩላቸው የክልሉ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋም የፋይናንስ አካታችነትን በመከተል ስራ አጥ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል።
በተለይም ተቋሙ የገንዘብ አቅሙን በማጠናከር ዘላቂ፣ ተደራሽና ፈጣን የሆነ አገልግሎት ለመስጠት አዳዲስ የአሰራር ስርዓቶችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የዛሬው ዐውደ ጥናት ዓላማም ባለድርሻ አካላት በተቋሙ አዳዲስ መመሪያዎች ዙሪያ በቂ ግንዛቤ በመያዝ የአጋርነታቸውን ሚና እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።
በዐውደ ጥናቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የተቋሙ የቦርድ አባላት፣ የዞንና የወረዳ የዘርፉ አመራሮችና አጋር አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026