አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ሕገ ወጥ ተግባራትን በመቆጣጠርና የምርት አቅርቦትን በማሻሻል ገበያውን የማረጋጋት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ተናገሩ::
ሚኒስትሩ ከሸቀጦች አቅርቦት እና ገበያውን ከማረጋጋት ጋር በተያያዘ እየተከናወኑ የሚገኙ ሥራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ለሸቀጦች ዋጋ መናር ምክንያት ከሆኑ ጉዳዮች መካከል የአቅርቦትና ፍላጎት አለመጣጣም ዋነኛው በመሆኑ ችግሩን ለመፍታት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የግብርና ምርቶችን ጨምሮ መሰረታዊ ሸቀጦችን በተለያዩ አማራጮች ለህብረተሰቡ የማቅረብ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።
በመላ ሀገሪቱ ወደ ሥራ በገቡ 1 ሺህ 234 የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎች ለሸማቾች ምርቶችን የማቅረብ ስራዎች አበረታች ውጤቶች እየታየባቸው እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ዘመናዊ የገበያ ማዕከላትን ወደ ሥራ በማስገባትም የተለያዩ የግብርና ምርቶች በቀጥታ በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች የሚቀርብበት ሂደት ሌላው ተጨባጭ ውጤት የተገኘበት ነው ብለዋል።
የከተማ ግብርናን በማስፋፋት የአትክልትና እንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች በተሻለ መልኩ ለዜጎች እየቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ እንዳሉት ከምርት አቅርቦት ጎን ለጎን ምርትን በመደበቅ፣ ሰው ሰራሽ እጥረት በመፍጠር እንዲሁም የተጋነነ ዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላት ላይ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው።
በሌላ በኩል መንግሥት በከፍተኛ ወጪ የሚያስገባውን የነዳጅ ምርት ስርጭት ላይ ጠንካራ ቁጥጥር እየተደረገ ነው ብለዋል።
ህገ ወጥ ድርጊት በሚፈጽሙ አካላት ላይም የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025