
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ሕገ ወጥ ተግባራትን በመቆጣጠርና የምርት አቅርቦትን በማሻሻል ገበያውን የማረጋጋት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ተናገሩ::
ሚኒስትሩ ከሸቀጦች አቅርቦት እና ገበያውን ከማረጋጋት ጋር በተያያዘ እየተከናወኑ የሚገኙ ሥራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ለሸቀጦች ዋጋ መናር ምክንያት ከሆኑ ጉዳዮች መካከል የአቅርቦትና ፍላጎት አለመጣጣም ዋነኛው በመሆኑ ችግሩን ለመፍታት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የግብርና ምርቶችን ጨምሮ መሰረታዊ ሸቀጦችን በተለያዩ አማራጮች ለህብረተሰቡ የማቅረብ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።
በመላ ሀገሪቱ ወደ ሥራ በገቡ 1 ሺህ 234 የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎች ለሸማቾች ምርቶችን የማቅረብ ስራዎች አበረታች ውጤቶች እየታየባቸው እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ዘመናዊ የገበያ ማዕከላትን ወደ ሥራ በማስገባትም የተለያዩ የግብርና ምርቶች በቀጥታ በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች የሚቀርብበት ሂደት ሌላው ተጨባጭ ውጤት የተገኘበት ነው ብለዋል።
የከተማ ግብርናን በማስፋፋት የአትክልትና እንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች በተሻለ መልኩ ለዜጎች እየቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ እንዳሉት ከምርት አቅርቦት ጎን ለጎን ምርትን በመደበቅ፣ ሰው ሰራሽ እጥረት በመፍጠር እንዲሁም የተጋነነ ዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላት ላይ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው።
በሌላ በኩል መንግሥት በከፍተኛ ወጪ የሚያስገባውን የነዳጅ ምርት ስርጭት ላይ ጠንካራ ቁጥጥር እየተደረገ ነው ብለዋል።
ህገ ወጥ ድርጊት በሚፈጽሙ አካላት ላይም የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026