የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>የገበያ ማረጋጋት እርምጃዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ- ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ሕገ ወጥ ተግባራትን በመቆጣጠርና የምርት አቅርቦትን በማሻሻል ገበያውን የማረጋጋት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ተናገሩ::

ሚኒስትሩ ከሸቀጦች አቅርቦት እና ገበያውን ከማረጋጋት ጋር በተያያዘ እየተከናወኑ የሚገኙ ሥራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ለሸቀጦች ዋጋ መናር ምክንያት ከሆኑ ጉዳዮች መካከል የአቅርቦትና ፍላጎት አለመጣጣም ዋነኛው በመሆኑ ችግሩን ለመፍታት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የግብርና ምርቶችን ጨምሮ መሰረታዊ ሸቀጦችን በተለያዩ አማራጮች ለህብረተሰቡ የማቅረብ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።

በመላ ሀገሪቱ ወደ ሥራ በገቡ 1 ሺህ 234 የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎች ለሸማቾች ምርቶችን የማቅረብ ስራዎች አበረታች ውጤቶች እየታየባቸው እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ዘመናዊ የገበያ ማዕከላትን ወደ ሥራ በማስገባትም የተለያዩ የግብርና ምርቶች በቀጥታ በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች የሚቀርብበት ሂደት ሌላው ተጨባጭ ውጤት የተገኘበት ነው ብለዋል።

የከተማ ግብርናን በማስፋፋት የአትክልትና እንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች በተሻለ መልኩ ለዜጎች እየቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ እንዳሉት ከምርት አቅርቦት ጎን ለጎን ምርትን በመደበቅ፣ ሰው ሰራሽ እጥረት በመፍጠር እንዲሁም የተጋነነ ዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላት ላይ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው።

በሌላ በኩል መንግሥት በከፍተኛ ወጪ የሚያስገባውን የነዳጅ ምርት ስርጭት ላይ ጠንካራ ቁጥጥር እየተደረገ ነው ብለዋል።

ህገ ወጥ ድርጊት በሚፈጽሙ አካላት ላይም የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026