
መቀሌ፤ የካቲት 21/2017 (ኢዜአ)፦ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር በሚያሰራጩ አካላት ላይ ቁጥጥር እና የሕግ ተጠያቂነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ኢዜአ ያነጋገራቸው የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተናገሩ።
በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጩ ሃሰተኛ መረጃዎች ዓለም ላይ ፈተና እየሆኑ መምጣታቸው ችግሩን ለመከላከል አገራት የየራሳቸውን ጥረት እያደረጉ ነው።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንም በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጭን ሃሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ለመከላከል መንግስት ጥብቅ ቁጥጥር ሊያደርግ እንደሚገባ ገልጸዋል።
በዩኒቨርሲቲው የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር መምህርና የስነ-ህዝብ ተመራማሪ ዳንኤል ግርማይ፤ በማህበራዊ ሚዲያ የሚተላለፉ ሀሰተኛ መረጃዎችና ጥላቻ ንግግሮች ለግጭትና አለመረጋጋት መንስዔ እንደሆኑ አንስተዋል።
በተለይም በውጭ አገራት ተቀምጠው ሀሰተኛ መረጃዎችና የጥላቻ ንግግሮችን በስፋት የሚያስተጋቡ አካላት እንዳሉ ጠቁመዋል።
ማህበራዊ ሚዲያን ለሀገር ልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት በሚበጁ አወንታዊ ተግባራት መጠቀም እንደሚገባ አንስተዋል።
ዜጎች በማህበራዊ ሚዲያ ከሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች መጠበቅ እንደሚገባቸው ጠቅሰው፤ በአንጻሩ መንግስት ሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
በዩኒቨርሲቲው የዓለም አቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ መምህር ገብረእግዚአብሄር ሀፍቱ፤ በርካታ ተከታይ ያላቸው አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተዋኒያን ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችን እንደሚያስተላለፉ ገልጸዋል።
በመሆኑም ሀሰተኛ መረጃዎች ሰላምን የሚያውኩ አካላትን ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ እና የሕግ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ይገባል ነው ያሉት።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026