መቀሌ፤ የካቲት 21/2017 (ኢዜአ)፦ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር በሚያሰራጩ አካላት ላይ ቁጥጥር እና የሕግ ተጠያቂነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ኢዜአ ያነጋገራቸው የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተናገሩ።
በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጩ ሃሰተኛ መረጃዎች ዓለም ላይ ፈተና እየሆኑ መምጣታቸው ችግሩን ለመከላከል አገራት የየራሳቸውን ጥረት እያደረጉ ነው።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንም በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጭን ሃሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ለመከላከል መንግስት ጥብቅ ቁጥጥር ሊያደርግ እንደሚገባ ገልጸዋል።
በዩኒቨርሲቲው የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር መምህርና የስነ-ህዝብ ተመራማሪ ዳንኤል ግርማይ፤ በማህበራዊ ሚዲያ የሚተላለፉ ሀሰተኛ መረጃዎችና ጥላቻ ንግግሮች ለግጭትና አለመረጋጋት መንስዔ እንደሆኑ አንስተዋል።
በተለይም በውጭ አገራት ተቀምጠው ሀሰተኛ መረጃዎችና የጥላቻ ንግግሮችን በስፋት የሚያስተጋቡ አካላት እንዳሉ ጠቁመዋል።
ማህበራዊ ሚዲያን ለሀገር ልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት በሚበጁ አወንታዊ ተግባራት መጠቀም እንደሚገባ አንስተዋል።
ዜጎች በማህበራዊ ሚዲያ ከሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች መጠበቅ እንደሚገባቸው ጠቅሰው፤ በአንጻሩ መንግስት ሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
በዩኒቨርሲቲው የዓለም አቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ መምህር ገብረእግዚአብሄር ሀፍቱ፤ በርካታ ተከታይ ያላቸው አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተዋኒያን ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችን እንደሚያስተላለፉ ገልጸዋል።
በመሆኑም ሀሰተኛ መረጃዎች ሰላምን የሚያውኩ አካላትን ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ እና የሕግ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ይገባል ነው ያሉት።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025