የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በማህበራዊ ሚዲያ ሃሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ አካላት ላይ ተጠያቂነት ማረጋገጥ ይገባል- ምሁራን</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ የካቲት 21/2017 (ኢዜአ)፦ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር በሚያሰራጩ አካላት ላይ ቁጥጥር እና የሕግ ተጠያቂነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ኢዜአ ያነጋገራቸው የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተናገሩ።

በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጩ ሃሰተኛ መረጃዎች ዓለም ላይ ፈተና እየሆኑ መምጣታቸው ችግሩን ለመከላከል አገራት የየራሳቸውን ጥረት እያደረጉ ነው።

ኢዜአ ያነጋገራቸው የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንም በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጭን ሃሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ለመከላከል መንግስት ጥብቅ ቁጥጥር ሊያደርግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በዩኒቨርሲቲው የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር መምህርና የስነ-ህዝብ ተመራማሪ ዳንኤል ግርማይ፤ በማህበራዊ ሚዲያ የሚተላለፉ ሀሰተኛ መረጃዎችና ጥላቻ ንግግሮች ለግጭትና አለመረጋጋት መንስዔ እንደሆኑ አንስተዋል።

በተለይም በውጭ አገራት ተቀምጠው ሀሰተኛ መረጃዎችና የጥላቻ ንግግሮችን በስፋት የሚያስተጋቡ አካላት እንዳሉ ጠቁመዋል።

ማህበራዊ ሚዲያን ለሀገር ልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት በሚበጁ አወንታዊ ተግባራት መጠቀም እንደሚገባ አንስተዋል።

ዜጎች በማህበራዊ ሚዲያ ከሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች መጠበቅ እንደሚገባቸው ጠቅሰው፤ በአንጻሩ መንግስት ሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

በዩኒቨርሲቲው የዓለም አቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ መምህር ገብረእግዚአብሄር ሀፍቱ፤ በርካታ ተከታይ ያላቸው አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተዋኒያን ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችን እንደሚያስተላለፉ ገልጸዋል።

በመሆኑም ሀሰተኛ መረጃዎች ሰላምን የሚያውኩ አካላትን ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ እና የሕግ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ይገባል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025