
መቀሌ፤ የካቲት 21/2017 (ኢዜአ)፦ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ሀሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር በሚያሰራጩ አካላት ላይ ቁጥጥር እና የሕግ ተጠያቂነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ኢዜአ ያነጋገራቸው የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተናገሩ።
በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጩ ሃሰተኛ መረጃዎች ዓለም ላይ ፈተና እየሆኑ መምጣታቸው ችግሩን ለመከላከል አገራት የየራሳቸውን ጥረት እያደረጉ ነው።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንም በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጭን ሃሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ለመከላከል መንግስት ጥብቅ ቁጥጥር ሊያደርግ እንደሚገባ ገልጸዋል።
በዩኒቨርሲቲው የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር መምህርና የስነ-ህዝብ ተመራማሪ ዳንኤል ግርማይ፤ በማህበራዊ ሚዲያ የሚተላለፉ ሀሰተኛ መረጃዎችና ጥላቻ ንግግሮች ለግጭትና አለመረጋጋት መንስዔ እንደሆኑ አንስተዋል።
በተለይም በውጭ አገራት ተቀምጠው ሀሰተኛ መረጃዎችና የጥላቻ ንግግሮችን በስፋት የሚያስተጋቡ አካላት እንዳሉ ጠቁመዋል።
ማህበራዊ ሚዲያን ለሀገር ልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት በሚበጁ አወንታዊ ተግባራት መጠቀም እንደሚገባ አንስተዋል።
ዜጎች በማህበራዊ ሚዲያ ከሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች መጠበቅ እንደሚገባቸው ጠቅሰው፤ በአንጻሩ መንግስት ሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
በዩኒቨርሲቲው የዓለም አቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ መምህር ገብረእግዚአብሄር ሀፍቱ፤ በርካታ ተከታይ ያላቸው አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተዋኒያን ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችን እንደሚያስተላለፉ ገልጸዋል።
በመሆኑም ሀሰተኛ መረጃዎች ሰላምን የሚያውኩ አካላትን ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ እና የሕግ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ይገባል ነው ያሉት።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025