የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር ፕሮጀክት ተቀርጾ ወደ ተግባር ተገብቷል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የማህበረሰብ ጥሪት ግንባታና የቤተሰብ ኑሮ ማሻሻያ ስራዎች ፕሮጀክት ተቀርጾ ወደ ትግበራ መገባቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) አስታወቁ።

በሁለት ዓመታት ውስጥ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ማሸጋገር የሚያስችል ግብ አስቀምጦ እየሰራ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

በክልሉ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር የማህበረሰብ ጥሪት ግንባታና የቤተሰብ ኑሮ ማሻሻያ ስራዎች ፕሮጀክት እቅድ ላይ የሚመክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡


በመድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሻው(ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ በቀጣይ ሁለት ዓመታት ውስጥ ምርታማነትን ማሳደግ የሚስችል ዕቅድ ተዘጋጅቷል።

በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት በማቋቋም ከተረጂነት ለማውጣት የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

መንግሥት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ ለማሳካት ተረጂ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት ማቋቋም የሚያስችል የበጀት ድጋፍ መደረጉን ገልፀዋል፡፡

በክልሉ ከተረጅነት ወደ ምርታማነት መሸጋገር የሚያስችልና ተፈፃሚ የሚሆን የፕሮጀክት እቅድና የበጀት ድልድል ለ35 ወረዳዎች መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።


በክልሉ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ ከግብ ለማድረስ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ገልፀዋል፡፡


የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ማዕረጉ ማቲዎስ በበኩላቸው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተጀመረው ጥረት እውን እንዲሆን በክልሉ የሚገኙ ተረጂዎችን ያሉበትን ደረጃ የማጥራት ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡

በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት በማቋቋም ከተረጂነት እንዲወጡ ማድረግ የሚያስችል እቅድ መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል፡፡

በክልሉ በሚገኙ 35 ወረዳዎች በተለይም ግብርናን መሰረት ባደረገ የስራ መስክ ለማሰማራት በጀት መመደቡንና ለተግባሩ ተፈፃሚነት የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት መፈፀሙን አስታውቀዋል።

በመርሐ ግብሩ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና ልዩ ወረዳ ከፍተኛ አመራር አካላት ተሳተፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026