የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር ፕሮጀክት ተቀርጾ ወደ ተግባር ተገብቷል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የማህበረሰብ ጥሪት ግንባታና የቤተሰብ ኑሮ ማሻሻያ ስራዎች ፕሮጀክት ተቀርጾ ወደ ትግበራ መገባቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) አስታወቁ።

በሁለት ዓመታት ውስጥ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ማሸጋገር የሚያስችል ግብ አስቀምጦ እየሰራ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

በክልሉ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር የማህበረሰብ ጥሪት ግንባታና የቤተሰብ ኑሮ ማሻሻያ ስራዎች ፕሮጀክት እቅድ ላይ የሚመክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡


በመድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሻው(ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ በቀጣይ ሁለት ዓመታት ውስጥ ምርታማነትን ማሳደግ የሚስችል ዕቅድ ተዘጋጅቷል።

በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት በማቋቋም ከተረጂነት ለማውጣት የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

መንግሥት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ ለማሳካት ተረጂ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት ማቋቋም የሚያስችል የበጀት ድጋፍ መደረጉን ገልፀዋል፡፡

በክልሉ ከተረጅነት ወደ ምርታማነት መሸጋገር የሚያስችልና ተፈፃሚ የሚሆን የፕሮጀክት እቅድና የበጀት ድልድል ለ35 ወረዳዎች መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።


በክልሉ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጉዞ ከግብ ለማድረስ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ገልፀዋል፡፡


የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ማዕረጉ ማቲዎስ በበኩላቸው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተጀመረው ጥረት እውን እንዲሆን በክልሉ የሚገኙ ተረጂዎችን ያሉበትን ደረጃ የማጥራት ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡

በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት በማቋቋም ከተረጂነት እንዲወጡ ማድረግ የሚያስችል እቅድ መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል፡፡

በክልሉ በሚገኙ 35 ወረዳዎች በተለይም ግብርናን መሰረት ባደረገ የስራ መስክ ለማሰማራት በጀት መመደቡንና ለተግባሩ ተፈፃሚነት የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት መፈፀሙን አስታውቀዋል።

በመርሐ ግብሩ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና ልዩ ወረዳ ከፍተኛ አመራር አካላት ተሳተፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026