አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ ከአራት ዓመት በፊት ከ50 ቢሊዮን ብር በታች የነበረው የኢትዮጵያ የዲጂታል የገንዘብ ዝውውር ወደ 9 ነጥብ 7 ትሪሊየን ብር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዲጂታል ሽግግርን ለማፋጠን ገቢራዊ የተደረገውን የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ቀድሞ ማሳካት ተችሏል፡፡
የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አንዱ ግብ ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ማድረግ በመሆኑ ስትራቴጂውን ቀድሞ ማሳካት እንዳስቻለ ጠቁመዋል።
በዚህም በተቀመጡ ቁልፍ መለኪያዎች መሰረት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን ቀድመን እየጨረስን ነው ብለዋል፡፡
ከመታወቂያ አገልግሎት ጀምሮ የግብይት ሥርዓቱ በቴሌ ብር፣ በሞባይል ባንኪንክ እና በሌሎች ዲጂታል አማራጮች እየተለመደ መምጣቱን አንስተዋል።
የፋይናንስ ስርዓቱን ጨምሮ በሁሉም ዘርፎች የኢትዮጵያን ዲጂታል ሽግግር ያፋጠኑ ስኬቶች መመዝገባቸውን ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል።
ለአብነትም በመንግሥት የኤሌክትሮኒክ ግዥ በዓለም አቀፍ መድረክ ተወዳዳሪ የሚያደርግ የዲጂታል ስርዓት መፈጠሩን ጠቅሰዋል።
በዚህም በኢትዮጵያ ከአራት ዓመት በፊት ከ50 ቢሊዬን ብር በታች የነበረው የዲጂታል ገንዘብ ዝውውር አሁን ላይ 9 ነጥብ 7 ትሪሊዬን ብር መድረሱን አብስረዋል።
የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል ኢትዮጵያን ከዘመኑ የኢንዱስትሪ አብዮት ተጠቃሚ የሚያደርግ የዲጂታል ስትራቴጂ እየተዘጋጀ ስለመሆኑ ገልጸዋል፡፡
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና የሚያሸጋግር የዲጂታል ስትራቴጂ በልፅጎ ገቢራዊ ይደረጋልም ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025