
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ ከአራት ዓመት በፊት ከ50 ቢሊዮን ብር በታች የነበረው የኢትዮጵያ የዲጂታል የገንዘብ ዝውውር ወደ 9 ነጥብ 7 ትሪሊየን ብር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዲጂታል ሽግግርን ለማፋጠን ገቢራዊ የተደረገውን የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ቀድሞ ማሳካት ተችሏል፡፡
የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አንዱ ግብ ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ማድረግ በመሆኑ ስትራቴጂውን ቀድሞ ማሳካት እንዳስቻለ ጠቁመዋል።
በዚህም በተቀመጡ ቁልፍ መለኪያዎች መሰረት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን ቀድመን እየጨረስን ነው ብለዋል፡፡
ከመታወቂያ አገልግሎት ጀምሮ የግብይት ሥርዓቱ በቴሌ ብር፣ በሞባይል ባንኪንክ እና በሌሎች ዲጂታል አማራጮች እየተለመደ መምጣቱን አንስተዋል።
የፋይናንስ ስርዓቱን ጨምሮ በሁሉም ዘርፎች የኢትዮጵያን ዲጂታል ሽግግር ያፋጠኑ ስኬቶች መመዝገባቸውን ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል።
ለአብነትም በመንግሥት የኤሌክትሮኒክ ግዥ በዓለም አቀፍ መድረክ ተወዳዳሪ የሚያደርግ የዲጂታል ስርዓት መፈጠሩን ጠቅሰዋል።
በዚህም በኢትዮጵያ ከአራት ዓመት በፊት ከ50 ቢሊዬን ብር በታች የነበረው የዲጂታል ገንዘብ ዝውውር አሁን ላይ 9 ነጥብ 7 ትሪሊዬን ብር መድረሱን አብስረዋል።
የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል ኢትዮጵያን ከዘመኑ የኢንዱስትሪ አብዮት ተጠቃሚ የሚያደርግ የዲጂታል ስትራቴጂ እየተዘጋጀ ስለመሆኑ ገልጸዋል፡፡
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና የሚያሸጋግር የዲጂታል ስትራቴጂ በልፅጎ ገቢራዊ ይደረጋልም ብለዋል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025