
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ ከአራት ዓመት በፊት ከ50 ቢሊዮን ብር በታች የነበረው የኢትዮጵያ የዲጂታል የገንዘብ ዝውውር ወደ 9 ነጥብ 7 ትሪሊየን ብር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዲጂታል ሽግግርን ለማፋጠን ገቢራዊ የተደረገውን የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ቀድሞ ማሳካት ተችሏል፡፡
የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አንዱ ግብ ዲጂታል ኢትዮጵያን ዕውን ማድረግ በመሆኑ ስትራቴጂውን ቀድሞ ማሳካት እንዳስቻለ ጠቁመዋል።
በዚህም በተቀመጡ ቁልፍ መለኪያዎች መሰረት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን ቀድመን እየጨረስን ነው ብለዋል፡፡
ከመታወቂያ አገልግሎት ጀምሮ የግብይት ሥርዓቱ በቴሌ ብር፣ በሞባይል ባንኪንክ እና በሌሎች ዲጂታል አማራጮች እየተለመደ መምጣቱን አንስተዋል።
የፋይናንስ ስርዓቱን ጨምሮ በሁሉም ዘርፎች የኢትዮጵያን ዲጂታል ሽግግር ያፋጠኑ ስኬቶች መመዝገባቸውን ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል።
ለአብነትም በመንግሥት የኤሌክትሮኒክ ግዥ በዓለም አቀፍ መድረክ ተወዳዳሪ የሚያደርግ የዲጂታል ስርዓት መፈጠሩን ጠቅሰዋል።
በዚህም በኢትዮጵያ ከአራት ዓመት በፊት ከ50 ቢሊዬን ብር በታች የነበረው የዲጂታል ገንዘብ ዝውውር አሁን ላይ 9 ነጥብ 7 ትሪሊዬን ብር መድረሱን አብስረዋል።
የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል ኢትዮጵያን ከዘመኑ የኢንዱስትሪ አብዮት ተጠቃሚ የሚያደርግ የዲጂታል ስትራቴጂ እየተዘጋጀ ስለመሆኑ ገልጸዋል፡፡
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና የሚያሸጋግር የዲጂታል ስትራቴጂ በልፅጎ ገቢራዊ ይደረጋልም ብለዋል፡፡
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026