የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>የተፋሰስ ልማቱ ብርቱ ተሳትፎ በመኸር እርሻም መደገም አለበት - ከንቲባ ከድር ጁሃር</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

ድሬደዋ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ በድሬደዋ አስተዳደር በተፋሰሰ ልማት ላይ የታየውን የተቀናጀ ብርቱ ተሳትፎ በመኸር እርሻ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ።

በድሬደዋ ገጠር ቀበሌዎች ለአንድ ወር የተካሄደው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል።

ከንቲባ ከድር ጁሃር በልማቱ ላይ ግንባር ቀደም ውጤት ላስመዘገቡ 12 ቀበሌዎች ዕውቅናና ሽልማት ሰጥተዋል።

ከንቲባው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ በተፋሰስ ልማት ላይ የታየው የተቀናጀ ውጤት በአጭር ጊዜ የገጠሩን ህብረተሰብ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እንደሚቻል ማሳያ ሆኗል።

በተፋሰስ ልማቱ የታየውን የተቀናጀ ተሳትፎ በመኸር እርሻም በመድገም የገጠሩን ህብረተሰብ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ መረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የድሬደዋ አስተዳደር ግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ በበኩላቸው ዘንድሮ በ5 ሺህ 550 ሄክታር መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈርና የውሃ ጥበቃ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በልማቱ ላይ ከ42 ሺህ በላይ የገጠር ነዋሪዎች በመሳተፍ 99 በመቶ የሚሆነውን ዕቅድ በላቀ ውጤት መፈፀማቸውን አስታውቀዋል።

በተከናወኑ ስራዎች ለተሳትፎ አካላት በሙሉ ዕውቅና የተሰጠ ሲሆን የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ደግሞ ትራክር እና የውሃ መሳቢያ ሞተር ጀነሬተር መበርከቱን ተናግረዋል።

በገጠር ቀበሌዎች ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025