
ድሬደዋ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ በድሬደዋ አስተዳደር በተፋሰሰ ልማት ላይ የታየውን የተቀናጀ ብርቱ ተሳትፎ በመኸር እርሻ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ።
በድሬደዋ ገጠር ቀበሌዎች ለአንድ ወር የተካሄደው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል።
ከንቲባ ከድር ጁሃር በልማቱ ላይ ግንባር ቀደም ውጤት ላስመዘገቡ 12 ቀበሌዎች ዕውቅናና ሽልማት ሰጥተዋል።
ከንቲባው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ በተፋሰስ ልማት ላይ የታየው የተቀናጀ ውጤት በአጭር ጊዜ የገጠሩን ህብረተሰብ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እንደሚቻል ማሳያ ሆኗል።
በተፋሰስ ልማቱ የታየውን የተቀናጀ ተሳትፎ በመኸር እርሻም በመድገም የገጠሩን ህብረተሰብ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ መረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የድሬደዋ አስተዳደር ግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ በበኩላቸው ዘንድሮ በ5 ሺህ 550 ሄክታር መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈርና የውሃ ጥበቃ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በልማቱ ላይ ከ42 ሺህ በላይ የገጠር ነዋሪዎች በመሳተፍ 99 በመቶ የሚሆነውን ዕቅድ በላቀ ውጤት መፈፀማቸውን አስታውቀዋል።
በተከናወኑ ስራዎች ለተሳትፎ አካላት በሙሉ ዕውቅና የተሰጠ ሲሆን የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ደግሞ ትራክር እና የውሃ መሳቢያ ሞተር ጀነሬተር መበርከቱን ተናግረዋል።
በገጠር ቀበሌዎች ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025