የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>የተፋሰስ ልማቱ ብርቱ ተሳትፎ በመኸር እርሻም መደገም አለበት - ከንቲባ ከድር ጁሃር</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

ድሬደዋ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ በድሬደዋ አስተዳደር በተፋሰሰ ልማት ላይ የታየውን የተቀናጀ ብርቱ ተሳትፎ በመኸር እርሻ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ።

በድሬደዋ ገጠር ቀበሌዎች ለአንድ ወር የተካሄደው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል።

ከንቲባ ከድር ጁሃር በልማቱ ላይ ግንባር ቀደም ውጤት ላስመዘገቡ 12 ቀበሌዎች ዕውቅናና ሽልማት ሰጥተዋል።

ከንቲባው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ በተፋሰስ ልማት ላይ የታየው የተቀናጀ ውጤት በአጭር ጊዜ የገጠሩን ህብረተሰብ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እንደሚቻል ማሳያ ሆኗል።

በተፋሰስ ልማቱ የታየውን የተቀናጀ ተሳትፎ በመኸር እርሻም በመድገም የገጠሩን ህብረተሰብ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ መረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የድሬደዋ አስተዳደር ግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ በበኩላቸው ዘንድሮ በ5 ሺህ 550 ሄክታር መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈርና የውሃ ጥበቃ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በልማቱ ላይ ከ42 ሺህ በላይ የገጠር ነዋሪዎች በመሳተፍ 99 በመቶ የሚሆነውን ዕቅድ በላቀ ውጤት መፈፀማቸውን አስታውቀዋል።

በተከናወኑ ስራዎች ለተሳትፎ አካላት በሙሉ ዕውቅና የተሰጠ ሲሆን የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ደግሞ ትራክር እና የውሃ መሳቢያ ሞተር ጀነሬተር መበርከቱን ተናግረዋል።

በገጠር ቀበሌዎች ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026