የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>የተፋሰስ ልማቱ ብርቱ ተሳትፎ በመኸር እርሻም መደገም አለበት - ከንቲባ ከድር ጁሃር</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

ድሬደዋ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ በድሬደዋ አስተዳደር በተፋሰሰ ልማት ላይ የታየውን የተቀናጀ ብርቱ ተሳትፎ በመኸር እርሻ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ።

በድሬደዋ ገጠር ቀበሌዎች ለአንድ ወር የተካሄደው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል።

ከንቲባ ከድር ጁሃር በልማቱ ላይ ግንባር ቀደም ውጤት ላስመዘገቡ 12 ቀበሌዎች ዕውቅናና ሽልማት ሰጥተዋል።

ከንቲባው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ በተፋሰስ ልማት ላይ የታየው የተቀናጀ ውጤት በአጭር ጊዜ የገጠሩን ህብረተሰብ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እንደሚቻል ማሳያ ሆኗል።

በተፋሰስ ልማቱ የታየውን የተቀናጀ ተሳትፎ በመኸር እርሻም በመድገም የገጠሩን ህብረተሰብ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ መረባረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የድሬደዋ አስተዳደር ግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ በበኩላቸው ዘንድሮ በ5 ሺህ 550 ሄክታር መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈርና የውሃ ጥበቃ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በልማቱ ላይ ከ42 ሺህ በላይ የገጠር ነዋሪዎች በመሳተፍ 99 በመቶ የሚሆነውን ዕቅድ በላቀ ውጤት መፈፀማቸውን አስታውቀዋል።

በተከናወኑ ስራዎች ለተሳትፎ አካላት በሙሉ ዕውቅና የተሰጠ ሲሆን የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ደግሞ ትራክር እና የውሃ መሳቢያ ሞተር ጀነሬተር መበርከቱን ተናግረዋል።

በገጠር ቀበሌዎች ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026