የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>የብራዚል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት መስክ እንዲሰማሩ ጥሪ ቀረበ</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፣ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ የብራዚል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ተጠቅመው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ጥሪ አቀረቡ።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ማስተዋወቂያ ፎረም በብራዚል መዲና ብራዚሊያ ተካሄዷል።


በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ፣ የብራዚል ኩባንያዎች፣ የንግድ ምክር ቤቶች እና የኢንዱስትሪ ፌዴሬሽኖች ተገኝተዋል።

ኩባንያዎቹ በግብርና ማቀነባበሪያ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን እና ቱሪዝም ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው።

አምባሳደር ምስጋኑ በፎረሙ ላይ ኢትዮጵያ በግብርና ማቀነባበሪያ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን ፣ቱሪዝም እንዲሁም በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽንስ ቴክኖሎጂ (አይ ሲቲ) ዘርፎች ትኩረት በሰጠቻቸው ጉዳዮች ዙሪያ ገለጻ አድርገዋል።

በኢትዮጵያ እየተደረገ ያለው ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ሪፎርም በኢትዮጵያ ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ መፍጠሩን አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ ያላት መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ፣ ሳቢ የኢንቨስትመንት ፓኬጆች፣ ምቹ ፖሊሲዎች፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች የገበያ ተደራሽነቱን ይበልጥ እንዳሰፋው አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገር መሆኗ እንዲሁም በአዲስ አበባ እና ሳኦ ፖሊ ከተሞች መካከል ያለው ዕለታዊ በረራ የብራዚል ባለሀብቶች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት መስክ እንዲሰማሩ ምቹ ዕድል የፈጠረ ነው ብለዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው የብራዚል ኩባንያዎች የኢትዮጵያን አዋጪ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ተጠቅመው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።

በፎረሙ ላይ የተሳተፉ የብራዚል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ተሳትፎ የማድረግ ፍላጎት እንዳደረባቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ እና ቱሪዝም ልውውጦች ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025