
አዲስ አበባ፣ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ የብራዚል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ተጠቅመው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ጥሪ አቀረቡ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ማስተዋወቂያ ፎረም በብራዚል መዲና ብራዚሊያ ተካሄዷል።

በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ፣ የብራዚል ኩባንያዎች፣ የንግድ ምክር ቤቶች እና የኢንዱስትሪ ፌዴሬሽኖች ተገኝተዋል።
ኩባንያዎቹ በግብርና ማቀነባበሪያ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን እና ቱሪዝም ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው።
አምባሳደር ምስጋኑ በፎረሙ ላይ ኢትዮጵያ በግብርና ማቀነባበሪያ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን ፣ቱሪዝም እንዲሁም በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽንስ ቴክኖሎጂ (አይ ሲቲ) ዘርፎች ትኩረት በሰጠቻቸው ጉዳዮች ዙሪያ ገለጻ አድርገዋል።
በኢትዮጵያ እየተደረገ ያለው ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ሪፎርም በኢትዮጵያ ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ መፍጠሩን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ ያላት መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ፣ ሳቢ የኢንቨስትመንት ፓኬጆች፣ ምቹ ፖሊሲዎች፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች የገበያ ተደራሽነቱን ይበልጥ እንዳሰፋው አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገር መሆኗ እንዲሁም በአዲስ አበባ እና ሳኦ ፖሊ ከተሞች መካከል ያለው ዕለታዊ በረራ የብራዚል ባለሀብቶች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት መስክ እንዲሰማሩ ምቹ ዕድል የፈጠረ ነው ብለዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው የብራዚል ኩባንያዎች የኢትዮጵያን አዋጪ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ተጠቅመው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።
በፎረሙ ላይ የተሳተፉ የብራዚል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ተሳትፎ የማድረግ ፍላጎት እንዳደረባቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ እና ቱሪዝም ልውውጦች ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026