
አዲስ አበባ፣ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ የብራዚል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ተጠቅመው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ጥሪ አቀረቡ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ማስተዋወቂያ ፎረም በብራዚል መዲና ብራዚሊያ ተካሄዷል።

በፎረሙ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ፣ የብራዚል ኩባንያዎች፣ የንግድ ምክር ቤቶች እና የኢንዱስትሪ ፌዴሬሽኖች ተገኝተዋል።
ኩባንያዎቹ በግብርና ማቀነባበሪያ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን እና ቱሪዝም ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው።
አምባሳደር ምስጋኑ በፎረሙ ላይ ኢትዮጵያ በግብርና ማቀነባበሪያ፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን ፣ቱሪዝም እንዲሁም በኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽንስ ቴክኖሎጂ (አይ ሲቲ) ዘርፎች ትኩረት በሰጠቻቸው ጉዳዮች ዙሪያ ገለጻ አድርገዋል።
በኢትዮጵያ እየተደረገ ያለው ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ሪፎርም በኢትዮጵያ ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ መፍጠሩን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ ያላት መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ፣ ሳቢ የኢንቨስትመንት ፓኬጆች፣ ምቹ ፖሊሲዎች፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች የገበያ ተደራሽነቱን ይበልጥ እንዳሰፋው አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገር መሆኗ እንዲሁም በአዲስ አበባ እና ሳኦ ፖሊ ከተሞች መካከል ያለው ዕለታዊ በረራ የብራዚል ባለሀብቶች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት መስክ እንዲሰማሩ ምቹ ዕድል የፈጠረ ነው ብለዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው የብራዚል ኩባንያዎች የኢትዮጵያን አዋጪ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ተጠቅመው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።
በፎረሙ ላይ የተሳተፉ የብራዚል ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ተሳትፎ የማድረግ ፍላጎት እንዳደረባቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ እና ቱሪዝም ልውውጦች ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026