አዳማ፤ የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፦ የግብርና ናሙና ቆጠራ በግብርና ሀብት ወሳኝ ግብዓቶችን በማሰባሰብ የዘርፉን ዘላቂ ዕድገት ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ተገለፀ።
ብሔራዊ የግብርና ናሙና ቆጠራ ሂደት የስድስት ወራት አፈፃፀምና ቀጣይ የሚካሄደው የግል እርሻዎች ቆጠራ ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ በአዳማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በቆጠራው የስታቲስቲክስ አገልግሎትን ጨምሮ የግብርና ሚኒስቴር፣ ፕላንና ልማት ሚኒስቴር፣ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩትና የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩትን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ተሳትፈዋል።
በመድረኩ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር) እንደገለፁት የግብርና ናሙና ቆጠራ ከ22 ዓመታት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ የግብርና ሀብቱ ያለበትን ሁኔታና ደረጃ ለማወቅ እየተካሄደ ይገኛል።
የመረጃ አሰባሰብ ታማኝነትና ትክክለኛነትን እውን ለማድረግ የቴክኒክና ሎጀስቲክ ድጋፍ በማድረግ በአገሪቱ ክልሎች የገጠር ቀበሌዎችና ከተሞች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
የግብርና ሚኒስትር ዲኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር)፤ ቆጠራው የግብርና ሀብት ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት የሚያስችል ነው ብለዋል።
በዚህም የግብርና ሀብቱ ያለበትን ደረጃና ሁኔታ በማወቅ ለዘርፉ ፖሊስና ስትራቴጂዎች በግብዓት በመጠቀም ግብርናን በሳይንሳዊ አሰራር ለመደገፍ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።
በቀጣይ የግብርና ሀብት ልማትና እድገት ዘላቂ ለማድረግ የሚያስችል ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ እንደሚገኝ አመላክተዋል።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍሰሃፅዮን በበኩላቸው በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ፣ ስትራቴጅና የልማት ፕሮግራምን ለማከናወን ቆጠራው ወሳኝ ነው ብለዋል።
የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ ለሀብት ምደባ፣ ለመሬት አጠቃቀም፣ ለሰብልና የእንስሳት ሀብት ልማት እድገት መረጃው አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወቅታዊ፣ ትክክለኛና አስተማማኝ የግብርና ሀብት መረጃ ወሳኝ ነው ብለዋል።
የአርሶ አደሮችን ምርትና ምርታማነት ለመጨመርና ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ፣ የኢኮኖሚ እድገት ለማስቀጠል ያስችላል።
እየተከሄደ ያለው የግብርና ናሙና ቆጠራና በቀጣይ ለሚከናወነው የግል እርሻዎች ቆጠራ ውጤታማነት በትብብር ይሰራል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025