የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>የግብርና ናሙና ቆጠራ የዘርፉን ዘላቂ ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ግብዓት ነው</p>

Mar 4, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፦ የግብርና ናሙና ቆጠራ በግብርና ሀብት ወሳኝ ግብዓቶችን በማሰባሰብ የዘርፉን ዘላቂ ዕድገት ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ተገለፀ።

ብሔራዊ የግብርና ናሙና ቆጠራ ሂደት የስድስት ወራት አፈፃፀምና ቀጣይ የሚካሄደው የግል እርሻዎች ቆጠራ ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ በአዳማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።


በቆጠራው የስታቲስቲክስ አገልግሎትን ጨምሮ የግብርና ሚኒስቴር፣ ፕላንና ልማት ሚኒስቴር፣ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩትና የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩትን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ተሳትፈዋል።

በመድረኩ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር) እንደገለፁት የግብርና ናሙና ቆጠራ ከ22 ዓመታት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ የግብርና ሀብቱ ያለበትን ሁኔታና ደረጃ ለማወቅ እየተካሄደ ይገኛል።

የመረጃ አሰባሰብ ታማኝነትና ትክክለኛነትን እውን ለማድረግ የቴክኒክና ሎጀስቲክ ድጋፍ በማድረግ በአገሪቱ ክልሎች የገጠር ቀበሌዎችና ከተሞች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የግብርና ሚኒስትር ዲኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር)፤ ቆጠራው የግብርና ሀብት ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት የሚያስችል ነው ብለዋል።


በዚህም የግብርና ሀብቱ ያለበትን ደረጃና ሁኔታ በማወቅ ለዘርፉ ፖሊስና ስትራቴጂዎች በግብዓት በመጠቀም ግብርናን በሳይንሳዊ አሰራር ለመደገፍ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።

በቀጣይ የግብርና ሀብት ልማትና እድገት ዘላቂ ለማድረግ የሚያስችል ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍሰሃፅዮን በበኩላቸው በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ፣ ስትራቴጅና የልማት ፕሮግራምን ለማከናወን ቆጠራው ወሳኝ ነው ብለዋል።


የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ ለሀብት ምደባ፣ ለመሬት አጠቃቀም፣ ለሰብልና የእንስሳት ሀብት ልማት እድገት መረጃው አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወቅታዊ፣ ትክክለኛና አስተማማኝ የግብርና ሀብት መረጃ ወሳኝ ነው ብለዋል።

የአርሶ አደሮችን ምርትና ምርታማነት ለመጨመርና ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ፣ የኢኮኖሚ እድገት ለማስቀጠል ያስችላል።

እየተከሄደ ያለው የግብርና ናሙና ቆጠራና በቀጣይ ለሚከናወነው የግል እርሻዎች ቆጠራ ውጤታማነት በትብብር ይሰራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026