
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያና አርጀንቲና በአቪዬሽን ዘርፍ ትብብራቸውን የበለጠ ለማጠናከር ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
በኢትዮጵያ የአርጀንቲና አምባሳደር ዡዋን ኢግናቺዮ ሮካታግሊያታ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንን ጎብኝተዋል።
አምባሳደሩ ከባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው መንግስቴ ጋር ተወያይተዋል።
ከአንድ ወር በፊት በአርጀንቲና ቦነስ አይረስ በተካሄደ ድርድር በአጭር ፊርማ ደረጃ የተጠናቀቀውን የአየር አገልግሎት ስምምነት በሙሉ ፊርማ ደረጃ የሚጠናቀቅበት ሂደት ማፋጠን ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል።
በአርጀንቲና በአውሮፕላን ማምረት፣ ጥገና፣ ምህንድስና የተሰማራው “FAdeA” ከተሰኘ ኩባንያ ጋር በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ አፍሪካን ታሳቢ ባደረገ መልኩ አዲስ አበባ ላይ ቅርንጫፍ በሚከፍትበት ሁኔታ እና ለባለስልጣኑ ድጋፍ በሚያደርግበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
በዓለም አቀፋ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት የሥራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ስብሰባ በሚቀርቡ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያም ተነጋግረዋል።
በአጭር ፊርማ ደረጃ ያለው የአየር አገልግሎት ስምምነት በሙሉ ፊርማ ደረጃ እንዲጠናቀቅ ሁለቱም ወገኞች የበኩላቸውን ጥረት ለማድረግ ተስማምተዋል።
“FAdeA” የተባለው የአርጀንቲና አውሮፕላን አምራችና የጥገና ኩባንያ በኢትዮጵያ ቅርንጫፍ የሚከፍትበትን ሁኔታ ለመወሰን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የውይይት መድረክ እንዲመቻች መግባባት ላይ መደረሱን ከባለስልጣኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025