
አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያና አርጀንቲና በአቪዬሽን ዘርፍ ትብብራቸውን የበለጠ ለማጠናከር ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
በኢትዮጵያ የአርጀንቲና አምባሳደር ዡዋን ኢግናቺዮ ሮካታግሊያታ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንን ጎብኝተዋል።
አምባሳደሩ ከባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው መንግስቴ ጋር ተወያይተዋል።
ከአንድ ወር በፊት በአርጀንቲና ቦነስ አይረስ በተካሄደ ድርድር በአጭር ፊርማ ደረጃ የተጠናቀቀውን የአየር አገልግሎት ስምምነት በሙሉ ፊርማ ደረጃ የሚጠናቀቅበት ሂደት ማፋጠን ላይ ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል።
በአርጀንቲና በአውሮፕላን ማምረት፣ ጥገና፣ ምህንድስና የተሰማራው “FAdeA” ከተሰኘ ኩባንያ ጋር በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ አፍሪካን ታሳቢ ባደረገ መልኩ አዲስ አበባ ላይ ቅርንጫፍ በሚከፍትበት ሁኔታ እና ለባለስልጣኑ ድጋፍ በሚያደርግበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።
በዓለም አቀፋ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት የሥራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ስብሰባ በሚቀርቡ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያም ተነጋግረዋል።
በአጭር ፊርማ ደረጃ ያለው የአየር አገልግሎት ስምምነት በሙሉ ፊርማ ደረጃ እንዲጠናቀቅ ሁለቱም ወገኞች የበኩላቸውን ጥረት ለማድረግ ተስማምተዋል።
“FAdeA” የተባለው የአርጀንቲና አውሮፕላን አምራችና የጥገና ኩባንያ በኢትዮጵያ ቅርንጫፍ የሚከፍትበትን ሁኔታ ለመወሰን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የውይይት መድረክ እንዲመቻች መግባባት ላይ መደረሱን ከባለስልጣኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026