
አዲስ አበባ፤የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፡- የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም (FSRP) አፈጻጸም ላይ የሚመከር ከፍተኛ የምክክር መድረክ ከነገ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይደረጋል።
ሁነቱን የዓለም ባንክ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን፣ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና የደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል (CCARDESA) በጋራ በመሆን ያዘጋጀው ነው።
የከፍተኛ ምክክር መድረኩ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ቀጣናዎች እየተተገበረ የሚገኘው የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም (FSRP) አፈጻጸም ላይ እንደሚወያይ ኢዜአ ከኢጋድ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካን የምግብ ስርዓት በዲጂታል ቴክኖሎጂዎች የማጠናከር ስራዎች ላይ ያጋጠሙ ፈናተዎች፣እድሎች እና አፈጻጸሙን የሚያሻሽሉ ስትራቴጂዎች ላይ ምክክር ይደረጋል።
የንግድ ትስስር እና የግብርና ፖሊሲዎች፣ ምርቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ የማድረግ ስራዎች እና ተቋማዊ የመፈጸም አቅምን ማጎልበት ሌሎች ውይይት የሚደረግባቸው አጀንዳዎች ናቸው።
የዓለም ባንክ የማይበገር የምግብ ስርዓት ኢንቨስትመንት እና ፕሮግራሙን እየተገበሩ ያሉ ሀገራት ተሞክሮዎች በውይይቱ ላይ ይቀርባሉ።
የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም ከፍተኛ የምክክር መድረክ እስከ የካቲት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026