የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>የማይበገር የምግብ ስርዓት ላይ ያተኮረ አህጉራዊ ምክክር በአዲስ አበባ ይካሄዳል</p>

Mar 4, 2025

IDOPRESS


አዲስ አበባ፤የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፡- የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም (FSRP) አፈጻጸም ላይ የሚመከር ከፍተኛ የምክክር መድረክ ከነገ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይደረጋል።


ሁነቱን የዓለም ባንክ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን፣ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና የደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል (CCARDESA) በጋራ በመሆን ያዘጋጀው ነው።


የከፍተኛ ምክክር መድረኩ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ቀጣናዎች እየተተገበረ የሚገኘው የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም (FSRP) አፈጻጸም ላይ እንደሚወያይ ኢዜአ ከኢጋድ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።


የአፍሪካን የምግብ ስርዓት በዲጂታል ቴክኖሎጂዎች የማጠናከር ስራዎች ላይ ያጋጠሙ ፈናተዎች፣እድሎች እና አፈጻጸሙን የሚያሻሽሉ ስትራቴጂዎች ላይ ምክክር ይደረጋል።


የንግድ ትስስር እና የግብርና ፖሊሲዎች፣ ምርቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ የማድረግ ስራዎች እና ተቋማዊ የመፈጸም አቅምን ማጎልበት ሌሎች ውይይት የሚደረግባቸው አጀንዳዎች ናቸው።


የዓለም ባንክ የማይበገር የምግብ ስርዓት ኢንቨስትመንት እና ፕሮግራሙን እየተገበሩ ያሉ ሀገራት ተሞክሮዎች በውይይቱ ላይ ይቀርባሉ።


የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም ከፍተኛ የምክክር መድረክ እስከ የካቲት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025