
አዲስ አበባ፤የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፡- የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም (FSRP) አፈጻጸም ላይ የሚመከር ከፍተኛ የምክክር መድረክ ከነገ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይደረጋል።
ሁነቱን የዓለም ባንክ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን፣ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና የደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል (CCARDESA) በጋራ በመሆን ያዘጋጀው ነው።
የከፍተኛ ምክክር መድረኩ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ቀጣናዎች እየተተገበረ የሚገኘው የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም (FSRP) አፈጻጸም ላይ እንደሚወያይ ኢዜአ ከኢጋድ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካን የምግብ ስርዓት በዲጂታል ቴክኖሎጂዎች የማጠናከር ስራዎች ላይ ያጋጠሙ ፈናተዎች፣እድሎች እና አፈጻጸሙን የሚያሻሽሉ ስትራቴጂዎች ላይ ምክክር ይደረጋል።
የንግድ ትስስር እና የግብርና ፖሊሲዎች፣ ምርቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ የማድረግ ስራዎች እና ተቋማዊ የመፈጸም አቅምን ማጎልበት ሌሎች ውይይት የሚደረግባቸው አጀንዳዎች ናቸው።
የዓለም ባንክ የማይበገር የምግብ ስርዓት ኢንቨስትመንት እና ፕሮግራሙን እየተገበሩ ያሉ ሀገራት ተሞክሮዎች በውይይቱ ላይ ይቀርባሉ።
የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም ከፍተኛ የምክክር መድረክ እስከ የካቲት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025