
አዲስ አበባ፤የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፡- የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም (FSRP) አፈጻጸም ላይ የሚመከር ከፍተኛ የምክክር መድረክ ከነገ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይደረጋል።
ሁነቱን የዓለም ባንክ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን፣ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና የደቡባዊ አፍሪካ የግብርና ምርምር እና ልማት ማስተባበሪያ ማዕከል (CCARDESA) በጋራ በመሆን ያዘጋጀው ነው።
የከፍተኛ ምክክር መድረኩ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ ቀጣናዎች እየተተገበረ የሚገኘው የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም (FSRP) አፈጻጸም ላይ እንደሚወያይ ኢዜአ ከኢጋድ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአፍሪካን የምግብ ስርዓት በዲጂታል ቴክኖሎጂዎች የማጠናከር ስራዎች ላይ ያጋጠሙ ፈናተዎች፣እድሎች እና አፈጻጸሙን የሚያሻሽሉ ስትራቴጂዎች ላይ ምክክር ይደረጋል።
የንግድ ትስስር እና የግብርና ፖሊሲዎች፣ ምርቶች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ የማድረግ ስራዎች እና ተቋማዊ የመፈጸም አቅምን ማጎልበት ሌሎች ውይይት የሚደረግባቸው አጀንዳዎች ናቸው።
የዓለም ባንክ የማይበገር የምግብ ስርዓት ኢንቨስትመንት እና ፕሮግራሙን እየተገበሩ ያሉ ሀገራት ተሞክሮዎች በውይይቱ ላይ ይቀርባሉ።
የማይበገር የምግብ ስርዓት ፕሮግራም ከፍተኛ የምክክር መድረክ እስከ የካቲት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026