
አዲስ አበባ ፤የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያና የደቡብ ሱዳን የድንበር ንግድ የጋራ ኮሚቴ የመጀመሪያ ስብሰባውን በቢሾፍቱ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
የንግድ ትስስርና የወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ያስሚን ውሃብረቢ እንደገለፁት፥ በስብሰባው ሁለቱ ሀገራት የተፈራረሙት የድንበር ንግድ ፕሮቶኮል አፈፃፀም ያለበትን ደረጃ እንደሚገመገም ገልጸዋል።
በቀጣይ ስምምነቱን በመተግበር የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር እንደሚደረግ አመልክተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታዋ፥ ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም የድንበር ንግድ ፕሮቶኮል መፈራረማቸውን አውስተዋል።
ስምምነቱ በድንበር አካባቢ ለሚኖሩ ለሁለቱም ህዝቦች መሰረታዊ የሆኑ የንግድ እቃዎችን ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የሁለቱ ሀገራት ህዝቦችን በኢኮኖሚ በማስተሳሰር እንዲሁም በድንበር አካባቢ ሠላምና መረጋጋትን በመፍጠር በኩል ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው ነው የገለጹት።
የጋራ ውይይትንና ትብብርን የሚጠይቁ እንዲሁም የድንበር ንግድ ፕሮቶኮል ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ እንደ ኮንትሮባንድ፣ህገ ወጥ ንግድ እና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ጥቅም ለደቡብ ሱዳን ጥቅም ነው፤ የደቡብ ሱዳን ጥቅም የኢትዮጵያም ጥቅም ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፥ ለጋራ ጥቅም በትብብር በጋራ መስራት እንደሚገባ መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025