
አዲስ አበባ ፤የካቲት 24/2017(ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያና የደቡብ ሱዳን የድንበር ንግድ የጋራ ኮሚቴ የመጀመሪያ ስብሰባውን በቢሾፍቱ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
የንግድ ትስስርና የወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ያስሚን ውሃብረቢ እንደገለፁት፥ በስብሰባው ሁለቱ ሀገራት የተፈራረሙት የድንበር ንግድ ፕሮቶኮል አፈፃፀም ያለበትን ደረጃ እንደሚገመገም ገልጸዋል።
በቀጣይ ስምምነቱን በመተግበር የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር እንደሚደረግ አመልክተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታዋ፥ ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን በየካቲት ወር 2017 ዓ.ም የድንበር ንግድ ፕሮቶኮል መፈራረማቸውን አውስተዋል።
ስምምነቱ በድንበር አካባቢ ለሚኖሩ ለሁለቱም ህዝቦች መሰረታዊ የሆኑ የንግድ እቃዎችን ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የሁለቱ ሀገራት ህዝቦችን በኢኮኖሚ በማስተሳሰር እንዲሁም በድንበር አካባቢ ሠላምና መረጋጋትን በመፍጠር በኩል ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው ነው የገለጹት።
የጋራ ውይይትንና ትብብርን የሚጠይቁ እንዲሁም የድንበር ንግድ ፕሮቶኮል ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ እንደ ኮንትሮባንድ፣ህገ ወጥ ንግድ እና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ጥቅም ለደቡብ ሱዳን ጥቅም ነው፤ የደቡብ ሱዳን ጥቅም የኢትዮጵያም ጥቅም ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፥ ለጋራ ጥቅም በትብብር በጋራ መስራት እንደሚገባ መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026