የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በክልሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ ለተቋማት የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው  </p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

ሮቤ፤ የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የአገልግሎት አሰጣጥን ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ በየደረጃው ለሚገኙ ተቋማት የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው ከባሌ ዞን አስተዳደር ጋር በመቀናጀት በወረዳና ቀበሌ ደረጃ ለሚገኙ አመራሮች የአቅም ግንባታ ሥልጠና በሮቤ ከተማ እየሰጠ ይገኛል።


በሥልጠናው ላይ የተገኙት የዩኒቨርስቲው ተመራማሪና ከፍተኛ አማካሪ ተሰማ አብዲሳ (ዶ/ር) እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው የክልሉ ህዝብ ከመንግስት የሚፈልገውን አገልግሎት እንዲያገኝ ጥናቶች ሲደረጉ ቆይቷል።

በተደረገው ጥናት መሰረትም የሚታዩ ተግዳሮቶችን በመለየት መፍትሄ እንዲያገኙ ከባለድርሻ አካላትጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይ ህዝቡ በተደጋጋሚ የሚያነሳቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ በየደረጃው የሚገኙ የአመራር አባላትን አቅም ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።

እንደ ከፍተኛ ተመራማሪው ገለጻ በታችኛው የመንግሥት መዋቅር ደረጃ የሚገኙ የአመራር አባላት በአካባቢያቸው የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችና አማራጮችን እንዲለዩ ሥልጠናው እገዛ እንደሚኖረው አክለዋል።

ሰልጣኞቹ በቆይታቸው በኢንተርፕሩነርሽፕና በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትኩረት ያደረጉ ሰነዶች ላይ ግንዛቤ እንዲያገኙ ይደረጋል ነው ያሉት።

የባሌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም ኃይሌ በበኩላቸው በዞኑ የሚገኙ 190 ቀበሌዎች በአዲስ አደረጃጀት ተዋቅረው ወደ ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል።

በዞኑ የቀበሌ አደረጃጀት አገልግሎት ተግባራዊ እንዲሆን ከ1 ሺህ 300 አመራሮች በላይ ተመድበው ህብረተሰቡን እንዲያገለግሉ መደረጉንም አስታውሰዋል፡፡

በአገልግሎቱም ከዚህ በፊት ወደ ዞንና ወረዳዎች በተደጋጋሚ ይመጡ የነበሩ ቅሬታዎች እየቀነሱ መምጣታቸውን አመልክተዋል።

በቀበሌ ደረጃ የተጀመረው የአገልግሎት አሰጣጥ ዘላቂ እንዲሆን በየአካባቢው ለተመደቡ አመራሮች እየተሰጠ የሚገኘው የአቅም ግንባታ ሥልጠና ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025