
ሮቤ፤ የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የአገልግሎት አሰጣጥን ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ በየደረጃው ለሚገኙ ተቋማት የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።
ዩኒቨርሲቲው ከባሌ ዞን አስተዳደር ጋር በመቀናጀት በወረዳና ቀበሌ ደረጃ ለሚገኙ አመራሮች የአቅም ግንባታ ሥልጠና በሮቤ ከተማ እየሰጠ ይገኛል።

በሥልጠናው ላይ የተገኙት የዩኒቨርስቲው ተመራማሪና ከፍተኛ አማካሪ ተሰማ አብዲሳ (ዶ/ር) እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው የክልሉ ህዝብ ከመንግስት የሚፈልገውን አገልግሎት እንዲያገኝ ጥናቶች ሲደረጉ ቆይቷል።
በተደረገው ጥናት መሰረትም የሚታዩ ተግዳሮቶችን በመለየት መፍትሄ እንዲያገኙ ከባለድርሻ አካላትጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይ ህዝቡ በተደጋጋሚ የሚያነሳቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ በየደረጃው የሚገኙ የአመራር አባላትን አቅም ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።
እንደ ከፍተኛ ተመራማሪው ገለጻ በታችኛው የመንግሥት መዋቅር ደረጃ የሚገኙ የአመራር አባላት በአካባቢያቸው የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችና አማራጮችን እንዲለዩ ሥልጠናው እገዛ እንደሚኖረው አክለዋል።
ሰልጣኞቹ በቆይታቸው በኢንተርፕሩነርሽፕና በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትኩረት ያደረጉ ሰነዶች ላይ ግንዛቤ እንዲያገኙ ይደረጋል ነው ያሉት።
የባሌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም ኃይሌ በበኩላቸው በዞኑ የሚገኙ 190 ቀበሌዎች በአዲስ አደረጃጀት ተዋቅረው ወደ ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል።
በዞኑ የቀበሌ አደረጃጀት አገልግሎት ተግባራዊ እንዲሆን ከ1 ሺህ 300 አመራሮች በላይ ተመድበው ህብረተሰቡን እንዲያገለግሉ መደረጉንም አስታውሰዋል፡፡
በአገልግሎቱም ከዚህ በፊት ወደ ዞንና ወረዳዎች በተደጋጋሚ ይመጡ የነበሩ ቅሬታዎች እየቀነሱ መምጣታቸውን አመልክተዋል።
በቀበሌ ደረጃ የተጀመረው የአገልግሎት አሰጣጥ ዘላቂ እንዲሆን በየአካባቢው ለተመደቡ አመራሮች እየተሰጠ የሚገኘው የአቅም ግንባታ ሥልጠና ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው ተናግረዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026