የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>በክልሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ ለተቋማት የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው  </p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

ሮቤ፤ የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የአገልግሎት አሰጣጥን ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ በየደረጃው ለሚገኙ ተቋማት የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው ከባሌ ዞን አስተዳደር ጋር በመቀናጀት በወረዳና ቀበሌ ደረጃ ለሚገኙ አመራሮች የአቅም ግንባታ ሥልጠና በሮቤ ከተማ እየሰጠ ይገኛል።


በሥልጠናው ላይ የተገኙት የዩኒቨርስቲው ተመራማሪና ከፍተኛ አማካሪ ተሰማ አብዲሳ (ዶ/ር) እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው የክልሉ ህዝብ ከመንግስት የሚፈልገውን አገልግሎት እንዲያገኝ ጥናቶች ሲደረጉ ቆይቷል።

በተደረገው ጥናት መሰረትም የሚታዩ ተግዳሮቶችን በመለየት መፍትሄ እንዲያገኙ ከባለድርሻ አካላትጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይ ህዝቡ በተደጋጋሚ የሚያነሳቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ በየደረጃው የሚገኙ የአመራር አባላትን አቅም ማጎልበት ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።

እንደ ከፍተኛ ተመራማሪው ገለጻ በታችኛው የመንግሥት መዋቅር ደረጃ የሚገኙ የአመራር አባላት በአካባቢያቸው የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችና አማራጮችን እንዲለዩ ሥልጠናው እገዛ እንደሚኖረው አክለዋል።

ሰልጣኞቹ በቆይታቸው በኢንተርፕሩነርሽፕና በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትኩረት ያደረጉ ሰነዶች ላይ ግንዛቤ እንዲያገኙ ይደረጋል ነው ያሉት።

የባሌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም ኃይሌ በበኩላቸው በዞኑ የሚገኙ 190 ቀበሌዎች በአዲስ አደረጃጀት ተዋቅረው ወደ ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል።

በዞኑ የቀበሌ አደረጃጀት አገልግሎት ተግባራዊ እንዲሆን ከ1 ሺህ 300 አመራሮች በላይ ተመድበው ህብረተሰቡን እንዲያገለግሉ መደረጉንም አስታውሰዋል፡፡

በአገልግሎቱም ከዚህ በፊት ወደ ዞንና ወረዳዎች በተደጋጋሚ ይመጡ የነበሩ ቅሬታዎች እየቀነሱ መምጣታቸውን አመልክተዋል።

በቀበሌ ደረጃ የተጀመረው የአገልግሎት አሰጣጥ ዘላቂ እንዲሆን በየአካባቢው ለተመደቡ አመራሮች እየተሰጠ የሚገኘው የአቅም ግንባታ ሥልጠና ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026