አዲስ አበባ፤የካቲት 25/2017(ኢዜአ)፦በካፒታል ገበያ የፋይናንስ ስርዓት ውስጥ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ገለጹ።
'የሴቶች የኢኮኖሚ አቅም ማጎልበት፣ በፋይናንስ ስርዓት ውስጥ የማካተት እና የካፒታል ገበያዎች' በሚል ርዕስ አለማቀፉን የሴቶች ቀን አስመልክቶ አውደጥናት ተካሒዷል።
ሚኒስትር ዴኤታዋ በወቅቱ እንዳሉት መንግስት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከመቼው ጊዜ በበለጠ እየሰራ ነው።
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የኢኮኖሚ እድገትን ይበልጥ ለማሳደግ የሚያስችሉ ስትራቴጂዎችን ቀርጻ እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህ ውስጥም ሴቶች ለአገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችሉ ስራዎች እንደሚገኙበት ተናግረዋል።
በቅርቡ የተጀመረው የካፒታል ገበያ ስርዓት ለሴት ሥራ ፈጣሪዎች የገንዘብ ድጋፍ ዕድሎችን በማቅረብ የንግድ ሥራ ዕድገትን እና ፈጠራን ለማጠናከር የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
መንግስት በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ይበልጥ አሳታፊና አካታች የኢኮኖሚ ስርዓትን ለመፍጠር ካቀደው ግብ ጋር ተያይዞ ለስርዓተ-ፆታ ምላሽ የሚሰጥ እቅድ አውጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት ሴቶች የኢኮኖሚ አቅማቸውን ለማሳደግና የሚያጋጥሟቸውን መሰናክሎች ለማሸነፍ በትብብር መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
የፋይናሻለ ሴክተር ዲፕኒግ ኢትዮጵያ(FSD) ዋና ስራ አስፈፃሚ ሒክመት አብደላ በበኩላቸው፥ የሴቶችን የፋይናሻል ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚሰሩ ተግባራት መጠናከር እንዳለባቸው አንስተዋል።
ፕሮግራሙ የተዘጋጀው አለም አቀፉን የሴቶችን ቀንን ከማክበር ባለፈ በፋይናንስ ዘርፉ በተሻለ መልኩ በመሳተፍ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል መሆኑን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቀት በፋይናንስ ዘርፉ ላይ የስርዓተ ጾታ ልዩነቶች ትኩረት የሚፈልጉ መሆኑን አንስተው ለዚህም የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ የፋይናሻል ተቋማት በትብብር መስራት ይገባቸዋል ብለዋል።
የዓለም ባንክ የኢንቨስትመንት ዋና ኃላፊ ግሬሲ ኪዩኮንዳ በበኩላቸው፤ ባንኩ አካታች የሆነ የዲጂታል ኢኮኖሚ መሰረተ ልማት ግንባታን ለመደገፍ ጠንካራ አቋም እንዳለው ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ የሴቶችን የፋይናንስ ተደራሽነት በማስፋትና ንግዱን በማሳደግ ክፍተቱን መዝጋት ይቻላል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025