የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ከተማ አስተዳደሩ በምግብ ዋስትና ፕሮግራም የታቀፉ ወገኖች ኑሮ ይበልጥ እንዲሻሻል ድጋፉን እንደሚቀጥል አስታወቀ

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- የአዳማ ከተማ አስተዳደር በምግብ ዋስትና ፕሮግራም የታቀፉ ወገኖች ኑሮ ይበልጥ እንዲሻሻል የሚያደርገውን ድጋፍና እገዛ እንደሚቀጥል የከተማው አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ ገለጹ።

በፕሮግራሙ ታቅፈው ባለፉት ሶስት ዓመታት በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ በመሰማራት ውጤታማ የሆኑ 2ሺህ 969 ወገኖች ዛሬ በአዳማ ተመርቀዋል።


እነዚህ ወገኖች በአካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ፣በከተማ ግብርና ፣ በተፋሰስ ልማት፣ በፅዳትና ውበት ስራዎች ላይ ተሰማርተው ሲሰሩ የቆዩ መሆናቸው ተመልክቷል።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ በወቅቱ፤ አስተዳደሩ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት መሻገር አለብን በሚል መርህ የተለያዩ ኢንሼቲቮችና የልማት ፕሮግራሞችን በመቅረጽ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

ተግባራዊ እየተደረጉ ካሉት ኢንሼቲቮች መካከል ሰፋፊ የስራ ዕድል መፍጠር የሚያስችሉ የወተት ላሞችና የዶሮ ዕርባታ፣ ንብ ማነብ፣ የስጋ ከብቶች ማድለብ፣ እርሻና ንግድ ስራዎች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል ።

በፕሮግራም ታቅፈው ውጤታማ የሆኑት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሆኑ አውሰተው፤ በቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ፣ ክህሎትና የቁጣባ ባህላቸው ዳብሮ ዛሬ ለምረቃ በቅተዋል ብለዋል ።

በተለይ በከተማዋ የስራ አጥነትን ለመቀነስና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተለያዩ ኢንሼቲቭ በመቅረጽ ከተረጂነትና ጠባቂነት ለማላቀቅ ከተማ አስተዳደሩ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።

በፕሮግራሙ ታቅፈው ውጤታማ በመሆን የተመረቁት ወገኖች ስራቸውን እንዲያጠናክሩ በስራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት በኩል ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ተግባር መግባቱን ከንቲባው አስታውቀዋል።


የአዳማ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ከዲጃ ጀማል በበኩላቸው፤ የምግብ ዋስትናን በከተማው ለማረጋገጥ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በከተማው የተለያዩ አካባቢዎች ተመልምለው በፕሮግራሙ የታቀፉ 2ሺህ 969 ወገኖች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ውጤታማ የሆኑትም የቁጠባ ባህል በማጎልበት በእንስሳት ማድለብ ፣ በወተት ልማት፣ በዶሮ እርባታ ፣ በንግድና በተለያዩ ሙያዎች ተሰማርተው ጠንከረው በመስራታቸው እንደሆነ አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026