
አዳማ ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- የአዳማ ከተማ አስተዳደር በምግብ ዋስትና ፕሮግራም የታቀፉ ወገኖች ኑሮ ይበልጥ እንዲሻሻል የሚያደርገውን ድጋፍና እገዛ እንደሚቀጥል የከተማው አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ ገለጹ።
በፕሮግራሙ ታቅፈው ባለፉት ሶስት ዓመታት በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ በመሰማራት ውጤታማ የሆኑ 2ሺህ 969 ወገኖች ዛሬ በአዳማ ተመርቀዋል።

እነዚህ ወገኖች በአካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ፣በከተማ ግብርና ፣ በተፋሰስ ልማት፣ በፅዳትና ውበት ስራዎች ላይ ተሰማርተው ሲሰሩ የቆዩ መሆናቸው ተመልክቷል።
የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ በወቅቱ፤ አስተዳደሩ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት መሻገር አለብን በሚል መርህ የተለያዩ ኢንሼቲቮችና የልማት ፕሮግራሞችን በመቅረጽ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።
ተግባራዊ እየተደረጉ ካሉት ኢንሼቲቮች መካከል ሰፋፊ የስራ ዕድል መፍጠር የሚያስችሉ የወተት ላሞችና የዶሮ ዕርባታ፣ ንብ ማነብ፣ የስጋ ከብቶች ማድለብ፣ እርሻና ንግድ ስራዎች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል ።
በፕሮግራም ታቅፈው ውጤታማ የሆኑት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሆኑ አውሰተው፤ በቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት ፣ ክህሎትና የቁጣባ ባህላቸው ዳብሮ ዛሬ ለምረቃ በቅተዋል ብለዋል ።
በተለይ በከተማዋ የስራ አጥነትን ለመቀነስና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተለያዩ ኢንሼቲቭ በመቅረጽ ከተረጂነትና ጠባቂነት ለማላቀቅ ከተማ አስተዳደሩ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።
በፕሮግራሙ ታቅፈው ውጤታማ በመሆን የተመረቁት ወገኖች ስራቸውን እንዲያጠናክሩ በስራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት በኩል ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ተግባር መግባቱን ከንቲባው አስታውቀዋል።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ከዲጃ ጀማል በበኩላቸው፤ የምግብ ዋስትናን በከተማው ለማረጋገጥ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
በከተማው የተለያዩ አካባቢዎች ተመልምለው በፕሮግራሙ የታቀፉ 2ሺህ 969 ወገኖች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ውጤታማ የሆኑትም የቁጠባ ባህል በማጎልበት በእንስሳት ማድለብ ፣ በወተት ልማት፣ በዶሮ እርባታ ፣ በንግድና በተለያዩ ሙያዎች ተሰማርተው ጠንከረው በመስራታቸው እንደሆነ አብራርተዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026