የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የሴቶችን አቅም በመገንባት በሁሉም ዘርፎች ንቁ ተሳትፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተሰራው ስራ አበረታች ነው

Mar 10, 2025

IDOPRESS

ሸገር፤ የካቲት 29/2017 (ኢዜአ)፡- የሴቶችን አቅም በመገንባት በሁሉም ዘርፎች ንቁ ተሳትፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ በተሰራው ስራ ውጤት ተመዝግቧል።


አለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ በሴቶች የለሙ የልማት ስራዎች ተጎብኝተዋል።


በበዓሉ ላይ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትርን ጨምሮ የኦሮሚያ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ፤ የሸገር ከተማ ከንቲባና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።


የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በሸገር ከተማ የተጎበኙት የሴቶች ልማት ስራዎች ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የስራ እድልን መፍጠር ያስቻሉ ናቸው።



ከዚህም ባለፈ ሴቶች በሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ፣ በመሪነት፣ በዲፕሎማሲ፤ በግጭት አፈታትና በሰላም ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።


የኦሮሚያ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መብራት ባጫ በበኩላቸው ሴቶች በክልሉ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ረገድ ንቁ ታሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ መሰራቱን ተናግረዋል።


ይህም በክልሉ የሴቶች ውሳኔ ሰጪነት እያደገ እንዲመጣና በለውጡ የራሳቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ ማስቻሉን አስታውቀዋል።


የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) በበኩላቸው አስተዳደሩ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም በመገንባት ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በትኩረት በመስራት ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።


በኢኮኖሚው ዘርፍ አስተዳደሩ የብድር አገልግሎትን በማመቻቸት በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ ተሰማርተው ራሳቸውን እንዲችሉ ማድረጉንም አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025