
ሸገር፤ የካቲት 29/2017 (ኢዜአ)፡- የሴቶችን አቅም በመገንባት በሁሉም ዘርፎች ንቁ ተሳትፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ በተሰራው ስራ ውጤት ተመዝግቧል።
አለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ በሴቶች የለሙ የልማት ስራዎች ተጎብኝተዋል።
በበዓሉ ላይ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትርን ጨምሮ የኦሮሚያ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ፤ የሸገር ከተማ ከንቲባና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በሸገር ከተማ የተጎበኙት የሴቶች ልማት ስራዎች ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የስራ እድልን መፍጠር ያስቻሉ ናቸው።

ከዚህም ባለፈ ሴቶች በሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ፣ በመሪነት፣ በዲፕሎማሲ፤ በግጭት አፈታትና በሰላም ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
የኦሮሚያ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ መብራት ባጫ በበኩላቸው ሴቶች በክልሉ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ረገድ ንቁ ታሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ መሰራቱን ተናግረዋል።
ይህም በክልሉ የሴቶች ውሳኔ ሰጪነት እያደገ እንዲመጣና በለውጡ የራሳቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ ማስቻሉን አስታውቀዋል።
የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) በበኩላቸው አስተዳደሩ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም በመገንባት ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በትኩረት በመስራት ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።
በኢኮኖሚው ዘርፍ አስተዳደሩ የብድር አገልግሎትን በማመቻቸት በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ ተሰማርተው ራሳቸውን እንዲችሉ ማድረጉንም አንስተዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026