የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በድሬዳዋ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለተሰማሩ አካላት የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል - የከተማ አስተዳደሩ

Mar 10, 2025

IDOPRESS

ድሬዳዋ፤ የካቲት 30/2017(ኢዜአ)፦ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ አካላትን የመሸጫና የማምረቻ ስፍራ ጥያቄዎች ለመመለስ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ።

በ20 ሚሊዮን ብር በጀት የተገነባው የመሸጫና የምርት ማሳያ ማዕከል በጥቃቅንና አነስተኛ ስራዎች ለተሰማሩ አምራቾች ዛሬ በዕጣ ተከፋፍሏል ።


የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አብዲ ሙክታር፤ በዕጣ ማውጣት ስነስርዓቱ ላይ እንደገለጹት አስተዳደሩ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በራስ አቅም የመመለስ ስራ አጠናክሮ ቀጥሏል።

በተለይም በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች የማምረቻና የመሸጫ ሼዶችን በመገንባት በርካታዎቹን ወደ ስራ ማስገባቱን አስታውቀዋል።

ከዚህ ጎን ለጎን በጥቃቅንና አነስተኛ ስራዎች የተሰማሩ ግለሰቦችን ጥያቄዎች ለመመለስ በከተማዋ የተለያዩ ስፍራዎች የገበያ ማዕከላት ገንብተው ለተጠቃሚዎች በማስተላለፍ ላይ መሆኑን አስረድተዋል።


በዛሬው ዕለት በ20 ሚሊዮን ብር የተገነባውና ለ29 ሰዎች የተላለፈው የገበያ ማዕከላት የዚሁ ጥረት ማሳያ መሆኑን በመግለፅ።

በቀጣይም የሌሎቹን ጥያቄዎች በተገቢው መንገድ ለመመለስ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ዕጣው የደረሳቸው ግለሰቦች በበኩላቸው በጀመሩት ሥራ ውጤታማ ለመሆን ጠንክረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።


ወጣት አብዱልከሪም ሁሴንና ወይዘሮ ዘኪያ ሙሳ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ራሳቸውን በመለወጥና ለሌሎች ሰዎች የስራ ዕድል ለመፍጠር እንደሚተጉ ገልጸዋል።

ዛሬ በተካሄደው የዕጣ ማውጣት ስነስርዓት ላይ 69 በጥቃቅንና አነስተኛ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ አካላት የተሳተፉ ሲሆን ዕጣ የወጣላቸው 29 ሰዎች የመሸጫና የምርት ማሳያ ማዕከል ተጠቃሚ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025