
ድሬዳዋ፤ የካቲት 30/2017(ኢዜአ)፦ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ አካላትን የመሸጫና የማምረቻ ስፍራ ጥያቄዎች ለመመለስ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ።
በ20 ሚሊዮን ብር በጀት የተገነባው የመሸጫና የምርት ማሳያ ማዕከል በጥቃቅንና አነስተኛ ስራዎች ለተሰማሩ አምራቾች ዛሬ በዕጣ ተከፋፍሏል ።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አብዲ ሙክታር፤ በዕጣ ማውጣት ስነስርዓቱ ላይ እንደገለጹት አስተዳደሩ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በራስ አቅም የመመለስ ስራ አጠናክሮ ቀጥሏል።
በተለይም በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች የማምረቻና የመሸጫ ሼዶችን በመገንባት በርካታዎቹን ወደ ስራ ማስገባቱን አስታውቀዋል።
ከዚህ ጎን ለጎን በጥቃቅንና አነስተኛ ስራዎች የተሰማሩ ግለሰቦችን ጥያቄዎች ለመመለስ በከተማዋ የተለያዩ ስፍራዎች የገበያ ማዕከላት ገንብተው ለተጠቃሚዎች በማስተላለፍ ላይ መሆኑን አስረድተዋል።

በዛሬው ዕለት በ20 ሚሊዮን ብር የተገነባውና ለ29 ሰዎች የተላለፈው የገበያ ማዕከላት የዚሁ ጥረት ማሳያ መሆኑን በመግለፅ።
በቀጣይም የሌሎቹን ጥያቄዎች በተገቢው መንገድ ለመመለስ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ዕጣው የደረሳቸው ግለሰቦች በበኩላቸው በጀመሩት ሥራ ውጤታማ ለመሆን ጠንክረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

ወጣት አብዱልከሪም ሁሴንና ወይዘሮ ዘኪያ ሙሳ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ራሳቸውን በመለወጥና ለሌሎች ሰዎች የስራ ዕድል ለመፍጠር እንደሚተጉ ገልጸዋል።
ዛሬ በተካሄደው የዕጣ ማውጣት ስነስርዓት ላይ 69 በጥቃቅንና አነስተኛ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ አካላት የተሳተፉ ሲሆን ዕጣ የወጣላቸው 29 ሰዎች የመሸጫና የምርት ማሳያ ማዕከል ተጠቃሚ ሆነዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025