
ድሬዳዋ፤ የካቲት 30/2017(ኢዜአ)፦ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ አካላትን የመሸጫና የማምረቻ ስፍራ ጥያቄዎች ለመመለስ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለፀ።
በ20 ሚሊዮን ብር በጀት የተገነባው የመሸጫና የምርት ማሳያ ማዕከል በጥቃቅንና አነስተኛ ስራዎች ለተሰማሩ አምራቾች ዛሬ በዕጣ ተከፋፍሏል ።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አብዲ ሙክታር፤ በዕጣ ማውጣት ስነስርዓቱ ላይ እንደገለጹት አስተዳደሩ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በመሰብሰብ የነዋሪውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በራስ አቅም የመመለስ ስራ አጠናክሮ ቀጥሏል።
በተለይም በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች የማምረቻና የመሸጫ ሼዶችን በመገንባት በርካታዎቹን ወደ ስራ ማስገባቱን አስታውቀዋል።
ከዚህ ጎን ለጎን በጥቃቅንና አነስተኛ ስራዎች የተሰማሩ ግለሰቦችን ጥያቄዎች ለመመለስ በከተማዋ የተለያዩ ስፍራዎች የገበያ ማዕከላት ገንብተው ለተጠቃሚዎች በማስተላለፍ ላይ መሆኑን አስረድተዋል።

በዛሬው ዕለት በ20 ሚሊዮን ብር የተገነባውና ለ29 ሰዎች የተላለፈው የገበያ ማዕከላት የዚሁ ጥረት ማሳያ መሆኑን በመግለፅ።
በቀጣይም የሌሎቹን ጥያቄዎች በተገቢው መንገድ ለመመለስ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ዕጣው የደረሳቸው ግለሰቦች በበኩላቸው በጀመሩት ሥራ ውጤታማ ለመሆን ጠንክረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

ወጣት አብዱልከሪም ሁሴንና ወይዘሮ ዘኪያ ሙሳ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ራሳቸውን በመለወጥና ለሌሎች ሰዎች የስራ ዕድል ለመፍጠር እንደሚተጉ ገልጸዋል።
ዛሬ በተካሄደው የዕጣ ማውጣት ስነስርዓት ላይ 69 በጥቃቅንና አነስተኛ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማሩ አካላት የተሳተፉ ሲሆን ዕጣ የወጣላቸው 29 ሰዎች የመሸጫና የምርት ማሳያ ማዕከል ተጠቃሚ ሆነዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026