የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

መከላከያ ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ከመወጣት ባለፈ ፕሮጀቶችን በጥራትና በፍጥነት ማጠናቀቅ የሚያስችል አቅም ፈጥሯል

Mar 11, 2025

IDOPRESS

ድሬዳዋ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- መከላከያ የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ከመወጣት ባለፈ ፕሮጀከቶችን በጥራትና በፍጥነት ማጠናቀቅ የሚያስችል ትልቅ አቅም መፍጠሩን በመከላከያ ሚኒስቴር የመሐንዲስ ዋና መምሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሌተናል ኮሎኔል ምስጋናው አያሌው ተናገሩ።

በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የስራ ተቋራጭነትና በመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ ባለቤትነት በድሬደዳዋ እና ጎዴ ከተሞች የተገነቡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ከነገ በስቲያ እንደሚመረቁ ተመላክቷል።

ሌተናል ኮሎኔል ምስጋናው አያሌው ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ሪፎርሙን ተከትሎ መከላከያ የተጣለበትን የሀገር ሉአላዊነትና ዳር ድንበር የማስከበር ተልዕኮ በላቀ ብቃት የመፈጸሙን ተግባር አጠናክሮ ቀጥሏል።

ከዚህ ጎን ለጎን የግንባታ ፕሮጀክቶችን በጥራት፣ በፍጥነትና በተያዘላቸው በጀት በማጠናቀቅ በሀገር ግንባታ ላይ የድርሻውን እያበረከተ መሆኑን በመጥቀስ።

ለአብነት በድሬዳዋና በጎዴ ከተሞች የገነባቸው ፕሮጀክቶች ተጠቃሽ የለውጥ ውጤቶች መሆናቸውን ሌተናል ኮሎኔል ምስጋናው ተናግረዋል።

እነዚህ ፕሮጀክቶች ከነገ በስትያ እንደሚመረቁ ጠቁመዋል።

መምሪያው በድሬዳዋ አስመርቆ ከሚያስረክባቸው ፕሮጀክቶች መካከል ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡት ከባለ አንድ መኝታ እስከ ባለ ሶስት መኝታ ክፍሎች ያላቸው 20 ባለ አራት ወለል የምስራቅ ዕዝ የመኖሪያ አፓርትመንት ይገኙበታል ብለዋል።

በተጨማሪም ለሠራዊቱ ዘመኑን የሚመጥን የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚችለው የምስራቅ ዕዝ ደረጃ ሶስት ሪፈራል ሆስፒታል ሌላኛው ፕሮጀክት መሆኑን ጠቅሰው፤ ቪላ ቤቶችን ያካተተው የምስራቅ ዕዝ የመኖሪያ መንደር እንደሚገኝበትም ገልፀዋል።

በጎዴ ከተማ የሚመረቁ ፕሮጀክቶች መኖራቸውንም ነው የገለጹት።

በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የድሬዳዋ አፓርትመንት ግንባታ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር እንዳልካቸው ታዬ በበኩላቸው፤ እስካሁን ባለው ሂደት ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡት 20 ብሎክ የመኖሪያ አፓርትመንት ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመላቸው ናቸው።

የአካባቢው የንግድ ማህበረሰብ በግንባታው ላይ በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ ሆኗል፤ ሠራዊቱም ከማህበረሰቡ ጋር ያለውን ፍቅርና አንድነት አፅንቶበታል ነው ያሉት።

በግንባታው ሂደትም ከሶስት ሺህ በላይ ሰዎች የስራ ዕድል ማግኘታቸውንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026