
ድሬዳዋ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- መከላከያ የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ከመወጣት ባለፈ ፕሮጀከቶችን በጥራትና በፍጥነት ማጠናቀቅ የሚያስችል ትልቅ አቅም መፍጠሩን በመከላከያ ሚኒስቴር የመሐንዲስ ዋና መምሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሌተናል ኮሎኔል ምስጋናው አያሌው ተናገሩ።
በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የስራ ተቋራጭነትና በመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ ባለቤትነት በድሬደዳዋ እና ጎዴ ከተሞች የተገነቡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ከነገ በስቲያ እንደሚመረቁ ተመላክቷል።
ሌተናል ኮሎኔል ምስጋናው አያሌው ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ሪፎርሙን ተከትሎ መከላከያ የተጣለበትን የሀገር ሉአላዊነትና ዳር ድንበር የማስከበር ተልዕኮ በላቀ ብቃት የመፈጸሙን ተግባር አጠናክሮ ቀጥሏል።
ከዚህ ጎን ለጎን የግንባታ ፕሮጀክቶችን በጥራት፣ በፍጥነትና በተያዘላቸው በጀት በማጠናቀቅ በሀገር ግንባታ ላይ የድርሻውን እያበረከተ መሆኑን በመጥቀስ።
ለአብነት በድሬዳዋና በጎዴ ከተሞች የገነባቸው ፕሮጀክቶች ተጠቃሽ የለውጥ ውጤቶች መሆናቸውን ሌተናል ኮሎኔል ምስጋናው ተናግረዋል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች ከነገ በስትያ እንደሚመረቁ ጠቁመዋል።
መምሪያው በድሬዳዋ አስመርቆ ከሚያስረክባቸው ፕሮጀክቶች መካከል ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡት ከባለ አንድ መኝታ እስከ ባለ ሶስት መኝታ ክፍሎች ያላቸው 20 ባለ አራት ወለል የምስራቅ ዕዝ የመኖሪያ አፓርትመንት ይገኙበታል ብለዋል።
በተጨማሪም ለሠራዊቱ ዘመኑን የሚመጥን የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚችለው የምስራቅ ዕዝ ደረጃ ሶስት ሪፈራል ሆስፒታል ሌላኛው ፕሮጀክት መሆኑን ጠቅሰው፤ ቪላ ቤቶችን ያካተተው የምስራቅ ዕዝ የመኖሪያ መንደር እንደሚገኝበትም ገልፀዋል።
በጎዴ ከተማ የሚመረቁ ፕሮጀክቶች መኖራቸውንም ነው የገለጹት።
በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የድሬዳዋ አፓርትመንት ግንባታ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር እንዳልካቸው ታዬ በበኩላቸው፤ እስካሁን ባለው ሂደት ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡት 20 ብሎክ የመኖሪያ አፓርትመንት ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመላቸው ናቸው።
የአካባቢው የንግድ ማህበረሰብ በግንባታው ላይ በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ ሆኗል፤ ሠራዊቱም ከማህበረሰቡ ጋር ያለውን ፍቅርና አንድነት አፅንቶበታል ነው ያሉት።
በግንባታው ሂደትም ከሶስት ሺህ በላይ ሰዎች የስራ ዕድል ማግኘታቸውንም ተናግረዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025