የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

መከላከያ ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ከመወጣት ባለፈ ፕሮጀቶችን በጥራትና በፍጥነት ማጠናቀቅ የሚያስችል አቅም ፈጥሯል

Mar 11, 2025

IDOPRESS

ድሬዳዋ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- መከላከያ የተጣለበትን ሀገራዊ ተልዕኮ በብቃት ከመወጣት ባለፈ ፕሮጀከቶችን በጥራትና በፍጥነት ማጠናቀቅ የሚያስችል ትልቅ አቅም መፍጠሩን በመከላከያ ሚኒስቴር የመሐንዲስ ዋና መምሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሌተናል ኮሎኔል ምስጋናው አያሌው ተናገሩ።

በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የስራ ተቋራጭነትና በመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ ባለቤትነት በድሬደዳዋ እና ጎዴ ከተሞች የተገነቡ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ከነገ በስቲያ እንደሚመረቁ ተመላክቷል።

ሌተናል ኮሎኔል ምስጋናው አያሌው ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ሪፎርሙን ተከትሎ መከላከያ የተጣለበትን የሀገር ሉአላዊነትና ዳር ድንበር የማስከበር ተልዕኮ በላቀ ብቃት የመፈጸሙን ተግባር አጠናክሮ ቀጥሏል።

ከዚህ ጎን ለጎን የግንባታ ፕሮጀክቶችን በጥራት፣ በፍጥነትና በተያዘላቸው በጀት በማጠናቀቅ በሀገር ግንባታ ላይ የድርሻውን እያበረከተ መሆኑን በመጥቀስ።

ለአብነት በድሬዳዋና በጎዴ ከተሞች የገነባቸው ፕሮጀክቶች ተጠቃሽ የለውጥ ውጤቶች መሆናቸውን ሌተናል ኮሎኔል ምስጋናው ተናግረዋል።

እነዚህ ፕሮጀክቶች ከነገ በስትያ እንደሚመረቁ ጠቁመዋል።

መምሪያው በድሬዳዋ አስመርቆ ከሚያስረክባቸው ፕሮጀክቶች መካከል ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡት ከባለ አንድ መኝታ እስከ ባለ ሶስት መኝታ ክፍሎች ያላቸው 20 ባለ አራት ወለል የምስራቅ ዕዝ የመኖሪያ አፓርትመንት ይገኙበታል ብለዋል።

በተጨማሪም ለሠራዊቱ ዘመኑን የሚመጥን የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚችለው የምስራቅ ዕዝ ደረጃ ሶስት ሪፈራል ሆስፒታል ሌላኛው ፕሮጀክት መሆኑን ጠቅሰው፤ ቪላ ቤቶችን ያካተተው የምስራቅ ዕዝ የመኖሪያ መንደር እንደሚገኝበትም ገልፀዋል።

በጎዴ ከተማ የሚመረቁ ፕሮጀክቶች መኖራቸውንም ነው የገለጹት።

በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የድሬዳዋ አፓርትመንት ግንባታ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር እንዳልካቸው ታዬ በበኩላቸው፤ እስካሁን ባለው ሂደት ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡት 20 ብሎክ የመኖሪያ አፓርትመንት ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመላቸው ናቸው።

የአካባቢው የንግድ ማህበረሰብ በግንባታው ላይ በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ ሆኗል፤ ሠራዊቱም ከማህበረሰቡ ጋር ያለውን ፍቅርና አንድነት አፅንቶበታል ነው ያሉት።

በግንባታው ሂደትም ከሶስት ሺህ በላይ ሰዎች የስራ ዕድል ማግኘታቸውንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026