የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

መገናኛ ብዙሃን የባህልና የጥበብ ስራዎችን በመጠቀም የአገር ገጽታን ሊያጎሉ ይገባል

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 03/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን የባህልና የጥበብ ስራዎችን በመጠቀም የአገር ገጽታን ሊያጎሉ እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ፡፡

ኢትዮጵያ "ባህልና ጥበባት ለቀጣናዊ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር" በሚል መሪ ሀሳብ ከመጪው መጋቢት 11 እስከ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ሁለተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የባህልና ጥበባት ፌስቲቫል ታዘጋጃለች።

ፌስቲቫሉን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።


በመድረኩ የተገኙት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ኢትዮጵያ በውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ ቅድሚያ ለጎረቤት ትሰጣለች ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገራት ጋር በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላት አንስተው፤ ይህን ትስስር የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል።

ከጎረቤት አገራት ጋር ያለውን ተመሳሳይ ባህል ለበጎ ተግባር መጠቀምና የቀጣናውን ልማት ማፋጠን እንደሚገባም አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገራት ጋር በመንገድ፣ በባቡር በኤሌክትሪክና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች ትስስር መፍጠሯ በጋራ የማደግ ፍላጎቷ ማሳያ ነው ብለዋል።

የቀጣናውን የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ባህልና ኪነ ጥበብ ቁልፍ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።

ባህልና ኪነ ጥበብ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን የበለጠ እንዲያጠናክሩ መገናኛ ብዙሃን ከተለመደው ዘገባ ባለፈ ጉዳዩን በጥልቀትና በስፋት መዘገብና ማስተዋወቅ አለባቸው ብለዋል።

መገናኛ ብዙሃን የአገርን ብሄራዊ ጥቅም በሚያስጠብቁ አጀንዳዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝና የአገርን ገፅታ የሚያስተዋውቁ ዘገባዎችን መስራት እንዳለባቸውም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026