
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 03/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን የባህልና የጥበብ ስራዎችን በመጠቀም የአገር ገጽታን ሊያጎሉ እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ፡፡
ኢትዮጵያ "ባህልና ጥበባት ለቀጣናዊ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር" በሚል መሪ ሀሳብ ከመጪው መጋቢት 11 እስከ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ሁለተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የባህልና ጥበባት ፌስቲቫል ታዘጋጃለች።
ፌስቲቫሉን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ የተገኙት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ኢትዮጵያ በውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ ቅድሚያ ለጎረቤት ትሰጣለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገራት ጋር በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላት አንስተው፤ ይህን ትስስር የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል።
ከጎረቤት አገራት ጋር ያለውን ተመሳሳይ ባህል ለበጎ ተግባር መጠቀምና የቀጣናውን ልማት ማፋጠን እንደሚገባም አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገራት ጋር በመንገድ፣ በባቡር በኤሌክትሪክና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች ትስስር መፍጠሯ በጋራ የማደግ ፍላጎቷ ማሳያ ነው ብለዋል።
የቀጣናውን የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ባህልና ኪነ ጥበብ ቁልፍ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።
ባህልና ኪነ ጥበብ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን የበለጠ እንዲያጠናክሩ መገናኛ ብዙሃን ከተለመደው ዘገባ ባለፈ ጉዳዩን በጥልቀትና በስፋት መዘገብና ማስተዋወቅ አለባቸው ብለዋል።
መገናኛ ብዙሃን የአገርን ብሄራዊ ጥቅም በሚያስጠብቁ አጀንዳዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝና የአገርን ገፅታ የሚያስተዋውቁ ዘገባዎችን መስራት እንዳለባቸውም አስታውቀዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025