
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 03/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን የባህልና የጥበብ ስራዎችን በመጠቀም የአገር ገጽታን ሊያጎሉ እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ፡፡
ኢትዮጵያ "ባህልና ጥበባት ለቀጣናዊ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር" በሚል መሪ ሀሳብ ከመጪው መጋቢት 11 እስከ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ሁለተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የባህልና ጥበባት ፌስቲቫል ታዘጋጃለች።
ፌስቲቫሉን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ የተገኙት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ኢትዮጵያ በውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ ቅድሚያ ለጎረቤት ትሰጣለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገራት ጋር በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላት አንስተው፤ ይህን ትስስር የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል።
ከጎረቤት አገራት ጋር ያለውን ተመሳሳይ ባህል ለበጎ ተግባር መጠቀምና የቀጣናውን ልማት ማፋጠን እንደሚገባም አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገራት ጋር በመንገድ፣ በባቡር በኤሌክትሪክና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች ትስስር መፍጠሯ በጋራ የማደግ ፍላጎቷ ማሳያ ነው ብለዋል።
የቀጣናውን የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ባህልና ኪነ ጥበብ ቁልፍ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።
ባህልና ኪነ ጥበብ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን የበለጠ እንዲያጠናክሩ መገናኛ ብዙሃን ከተለመደው ዘገባ ባለፈ ጉዳዩን በጥልቀትና በስፋት መዘገብና ማስተዋወቅ አለባቸው ብለዋል።
መገናኛ ብዙሃን የአገርን ብሄራዊ ጥቅም በሚያስጠብቁ አጀንዳዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝና የአገርን ገፅታ የሚያስተዋውቁ ዘገባዎችን መስራት እንዳለባቸውም አስታውቀዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026