የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

መገናኛ ብዙሃን የባህልና የጥበብ ስራዎችን በመጠቀም የአገር ገጽታን ሊያጎሉ ይገባል

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 03/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን የባህልና የጥበብ ስራዎችን በመጠቀም የአገር ገጽታን ሊያጎሉ እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ፡፡

ኢትዮጵያ "ባህልና ጥበባት ለቀጣናዊ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር" በሚል መሪ ሀሳብ ከመጪው መጋቢት 11 እስከ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ሁለተኛውን የምስራቅ አፍሪካ የባህልና ጥበባት ፌስቲቫል ታዘጋጃለች።

ፌስቲቫሉን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።


በመድረኩ የተገኙት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ኢትዮጵያ በውጭ ጉዳይ ፖሊሲዋ ቅድሚያ ለጎረቤት ትሰጣለች ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገራት ጋር በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላት አንስተው፤ ይህን ትስስር የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል።

ከጎረቤት አገራት ጋር ያለውን ተመሳሳይ ባህል ለበጎ ተግባር መጠቀምና የቀጣናውን ልማት ማፋጠን እንደሚገባም አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገራት ጋር በመንገድ፣ በባቡር በኤሌክትሪክና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች ትስስር መፍጠሯ በጋራ የማደግ ፍላጎቷ ማሳያ ነው ብለዋል።

የቀጣናውን የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ባህልና ኪነ ጥበብ ቁልፍ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።

ባህልና ኪነ ጥበብ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን የበለጠ እንዲያጠናክሩ መገናኛ ብዙሃን ከተለመደው ዘገባ ባለፈ ጉዳዩን በጥልቀትና በስፋት መዘገብና ማስተዋወቅ አለባቸው ብለዋል።

መገናኛ ብዙሃን የአገርን ብሄራዊ ጥቅም በሚያስጠብቁ አጀንዳዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝና የአገርን ገፅታ የሚያስተዋውቁ ዘገባዎችን መስራት እንዳለባቸውም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026