የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ቢሮው የመዲናዋን የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች በተመለከተ ከነዋሪዎች ጥሪ መቀበል የሚያስችል የጥሪ ማዕከል ስራ አስጀመረ

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ የመዲናዋን የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች በተመለከተ ከነዋሪዎች ጥሪ መቀበል የሚያስችል የጥሪ ማዕከልን ጨምሮ የተለያዩ 10 ቴክኖሎጂዎችን ይፋ አደርጓል።

ፀጥታን የተመለከቱ ጥቆማና ቅሬታ፣ በማንኛውም የከተማዋ የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ እና በቢሮው አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መረጃ መስጠት የሚያስችሉ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ነው ቢሮው ዛሬ ይፋ ያደረገው።


በዚህም ቢሮው 8882 የነፃ የስልክ ጥሪ ማዕከል፣ የድረ ገጽ፣ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ፣ አሴት ማኔጅመንት፣ ቪዲዮ ኮንፍረንስን ጨምሮ ሌሎች የቴክኖሎጂ ስራዎችን ይፋ አድርጓል።

ቢሮው የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ያለማቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለማስተዋወቅና ለማስጀመር የተዘጋጀ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በቢሮው የለሙትን ቴክኖሎጂዎች ይፋ ባደረጉበት ወቅት እንዳሉት ባለፉት ዓመታት ህዝቡን በማሳተፍ በተሰሩ ስራዎች የከተማዋን ሰላም ዘላቂ ማድረግ ተችሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025