
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ የመዲናዋን የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች በተመለከተ ከነዋሪዎች ጥሪ መቀበል የሚያስችል የጥሪ ማዕከልን ጨምሮ የተለያዩ 10 ቴክኖሎጂዎችን ይፋ አደርጓል።
ፀጥታን የተመለከቱ ጥቆማና ቅሬታ፣ በማንኛውም የከተማዋ የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ እና በቢሮው አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መረጃ መስጠት የሚያስችሉ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ነው ቢሮው ዛሬ ይፋ ያደረገው።

በዚህም ቢሮው 8882 የነፃ የስልክ ጥሪ ማዕከል፣ የድረ ገጽ፣ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ፣ አሴት ማኔጅመንት፣ ቪዲዮ ኮንፍረንስን ጨምሮ ሌሎች የቴክኖሎጂ ስራዎችን ይፋ አድርጓል።
ቢሮው የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ያለማቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለማስተዋወቅና ለማስጀመር የተዘጋጀ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በቢሮው የለሙትን ቴክኖሎጂዎች ይፋ ባደረጉበት ወቅት እንዳሉት ባለፉት ዓመታት ህዝቡን በማሳተፍ በተሰሩ ስራዎች የከተማዋን ሰላም ዘላቂ ማድረግ ተችሏል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026