የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ቢሮው የመዲናዋን የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች በተመለከተ ከነዋሪዎች ጥሪ መቀበል የሚያስችል የጥሪ ማዕከል ስራ አስጀመረ

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2017(ኢዜአ)፡- የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ የመዲናዋን የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች በተመለከተ ከነዋሪዎች ጥሪ መቀበል የሚያስችል የጥሪ ማዕከልን ጨምሮ የተለያዩ 10 ቴክኖሎጂዎችን ይፋ አደርጓል።

ፀጥታን የተመለከቱ ጥቆማና ቅሬታ፣ በማንኛውም የከተማዋ የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ እና በቢሮው አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መረጃ መስጠት የሚያስችሉ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ነው ቢሮው ዛሬ ይፋ ያደረገው።


በዚህም ቢሮው 8882 የነፃ የስልክ ጥሪ ማዕከል፣ የድረ ገጽ፣ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ፣ አሴት ማኔጅመንት፣ ቪዲዮ ኮንፍረንስን ጨምሮ ሌሎች የቴክኖሎጂ ስራዎችን ይፋ አድርጓል።

ቢሮው የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ያለማቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለማስተዋወቅና ለማስጀመር የተዘጋጀ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በቢሮው የለሙትን ቴክኖሎጂዎች ይፋ ባደረጉበት ወቅት እንዳሉት ባለፉት ዓመታት ህዝቡን በማሳተፍ በተሰሩ ስራዎች የከተማዋን ሰላም ዘላቂ ማድረግ ተችሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026