የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአዲስ አበባ ከተማ በ2ኛ ምዕራፍ እየለሙ የሚገኙ ስምንት ኮሪደሮች የስራ አፈጻጸም ተገመገመ

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ ከተማ በ2ኛ ምዕራፍ እየለሙ የሚገኙ ስምንት ኮሪደሮች የስራ አፈጻጸም መገምገሙን የመዲናዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ላለፉት ሁለት ቀናት ከሁሉም የኮሪደር ልማት አስተባባሪዎች ጋር በመሆን በ2ኛ ምዕራፍ በከተማችን እየለሙ የሚገኙ ስምንት ኮሪደሮችን የስራ አፈጻጸም ተዘዋውረን ገምግመናል ብለዋል።


የ2ኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራ 135 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው የመንገድ ግንባታ፣ 42 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራ፣ 431 ሄክታር የሚሸፍን የአረንጓዴ ልማት ስራ፣ በከተማችን ያለውን የትራንስፖርት ስርዓት ለማዘመን ከምንሰራው ስራ በተጨማሪ 23,320 በላይ መኪኖችን የማስቆም አቅም ያለው የፓርኪንግና ተርሚናሎች ግንባታ፣ 112 የህዝብ የመጸዳጃ ቦታዎች ግንባታ፣ 2669 ህንጻዎች እድሳት፣ የህጻናት መጫወቻ ሜዳዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ የህዝብ መዝናኛ ፕላዛዎች፣ የእግረኛ እና የብስክሌት መንገዶችን ያካተተ ሲሆን ከ62ሺሕ በላይ ለሚሆኑ የከተማችን ነዋሪዎች ደግሞ የስራ እድልን የፈጠረ ሰፊ ስራ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

ከተማውን በመበከል የህዝቡን ጤና በመጉዳት ከፍተኛ አሉታዊ ጉዳት ሲያደርሱ የነበሩትን ህግ እና ስርዓት አውጥተን የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓት በከፍተኛ ደረጃ እየተገበርን ነው ሲሉም አክለዋል።

የወንዞችን ብክለት በመከላከል በኩል ጽዱ አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ለመፍጠር የብክለት መከላከል ህግ ህብረተሰባችን መቀበሉን እና እየተገበረው መሆኑን በጉብኝታችን ወቅት ተመልክተናል ሲሉም ገልጸዋል።


በተሰጣቸው ጊዜ ገደብ ውስጥ ያልገነቡ እና የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓታቸውን ያላስተካከሉትን በመቅጣት ላይ የምንገኝ ሲሆን ከቅጣቱ በላይ የምንፈልገው ህዝባችን በዋናነት ለራሱ ጤና ሲል የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓቱን እና ብክለት መከላከልን እንዲተገብር በመሆኑ ሁላችንም ለዚህ ርብርብ እንድናደርግ ጥሪ አቀርባለሁ ብለዋል።

ያቀረብንላቸውን ጥሪ በመቀበል ህንጻዎችን በማደስ፣ ቀለም በመቀየር እና በከተማዋ ስታንዳርድ መሰረት መብራት በመዘርጋት እያገዙን የሚገኙ የከተማችን ነዋሪዎች፣ ባለሀብቶች እንዲሁም የመንግስትና የግል ተቋማትን ጨምሮ ሙያዊ እና ቁሳዊ ድጋፍ እያደረጉልን የሚገኙ ነዋሪዎቻችንን በራሴ እና በከተማ አስተዳደራችን ስም ላመሰግናቸው እወዳለሁ ነው ያሉት።

በቀሪ ጊዜያት ልዩ ክትትል በማድረግ ቶሎ መጠናቅ ያለባቸውን ስራዎች መጨረስ፣ መደገፍ የሚገባቸውን ደግሞ እየደገፍን ህዝባችንን በታማኝነት ለማገልገል በገባነው ቃል መሰረት 2ኛውን ምዕራፍ የኮሪደር ልማት አጠናቅቀን ለግልጋሎት ክፍት የምናደርግ ይሆናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025