አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በልግ አብቃይ አካባቢዎች ለበልግ እርሻ ልማት አንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ሄክታር መሬት መዘጋጀቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ባሪሶ ፋይሳ እንዳሉት በዘንድሮ የበልግ ወቅት አንድ ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማልማት ከ40 ሚሊዮን በላይ ኩንታል ምርት ለማግኘት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው።
በዚህ ወቅት በዘር ለመሸፈን ከታቀደው ውስጥ እስካሁን አንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ሄክታር መሬት መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
በዚህም በክልሉ በሁሉም በልግ አብቃይ በሆኑ ዞኖች የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር እየተጓጓዝ መሆኑን ገልጸዋል።
ቢሮው ባለፉት ዓመታት ከነበሩት ክፍተቶች ልምድ በመውሰድ ከባለሙያዎችና አርሶ አደሮች ጋር ውይይት ተደርጎ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።
በዚህም በዘንድሮ ዓመት ማሟላት የሚገቡ ክፍተቶች ተለይተው ወደ ስራ መገባቱን አመልክተው ቀጣይ ዘር መዝራትና የሰብል እንክብካቤና ጥበቃ ተከታታይ ስራዎች እንደሚሰሩም አስረድተዋል።
በዚህ ዓመት በተለየ ሁኔታ ከሁለተኛ ሩብ ዓመት ጀምሮ ከክልል እስከ ቀበሌ ድረስ በተካሄደ ግምገማ አርሶ አደሩን በማንቃት ጊዜውን በአግባቡ መጠቀም እንዲችል መደረጉንም አክለዋል።
በማሳ ዝግጅት፣ በአፈር ማዳበሪያ፣ በዘር አያያዝና አጠቃቀም፣ በሰብል እንክብካቤና ጥበቃ በኩል በተሰራው ስራ የአርሶ አደሩ መነቃቃትና ተነሳሽነት በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል።
አርሶ አደሩ አሁን ላይ ከባህላዊ ወደ ዘመናዊ የአስተራረስ ስነ-ዘዴ እየተሸጋገረ መምጣቱን አመልክተው ለዚህም 7 ሺህ ትራክተሮች እንዲገቡ መደረጉን አስታውቀዋል።
ትራክተሮቹም በየአካባቢዎቹ እየተንቀሳቀሱ የሚያርሱ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ አርሶ አደሮቹ በተፈጠረላቸው ምቹ ሁኔታ በኑሮው እየተለወጠ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተያዘው የበልግ ወቅት አርሶ አደሩ፣ ባለሙያውና አመራሩ ጊዜውን በአግባቡ በመጠቀም ባለው ዝናብ ዘር በመዝራትና በመንከባከብ በኩል ርብርብ ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025