የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በኦሮሚያ ክልል በበልግ ወቅት የሚለማ አንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ሄክታር መሬት ተዘጋጅቷል - የክልሉ ግብርና ቢሮ

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 4/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል በልግ አብቃይ አካባቢዎች ለበልግ እርሻ ልማት አንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ሄክታር መሬት መዘጋጀቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ባሪሶ ፋይሳ እንዳሉት በዘንድሮ የበልግ ወቅት አንድ ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማልማት ከ40 ሚሊዮን በላይ ኩንታል ምርት ለማግኘት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ነው።

በዚህ ወቅት በዘር ለመሸፈን ከታቀደው ውስጥ እስካሁን አንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ሄክታር መሬት መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

በዚህም በክልሉ በሁሉም በልግ አብቃይ በሆኑ ዞኖች የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር እየተጓጓዝ መሆኑን ገልጸዋል።

ቢሮው ባለፉት ዓመታት ከነበሩት ክፍተቶች ልምድ በመውሰድ ከባለሙያዎችና አርሶ አደሮች ጋር ውይይት ተደርጎ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

በዚህም በዘንድሮ ዓመት ማሟላት የሚገቡ ክፍተቶች ተለይተው ወደ ስራ መገባቱን አመልክተው ቀጣይ ዘር መዝራትና የሰብል እንክብካቤና ጥበቃ ተከታታይ ስራዎች እንደሚሰሩም አስረድተዋል።

በዚህ ዓመት በተለየ ሁኔታ ከሁለተኛ ሩብ ዓመት ጀምሮ ከክልል እስከ ቀበሌ ድረስ በተካሄደ ግምገማ አርሶ አደሩን በማንቃት ጊዜውን በአግባቡ መጠቀም እንዲችል መደረጉንም አክለዋል።

በማሳ ዝግጅት፣ በአፈር ማዳበሪያ፣ በዘር አያያዝና አጠቃቀም፣ በሰብል እንክብካቤና ጥበቃ በኩል በተሰራው ስራ የአርሶ አደሩ መነቃቃትና ተነሳሽነት በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል።

አርሶ አደሩ አሁን ላይ ከባህላዊ ወደ ዘመናዊ የአስተራረስ ስነ-ዘዴ እየተሸጋገረ መምጣቱን አመልክተው ለዚህም 7 ሺህ ትራክተሮች እንዲገቡ መደረጉን አስታውቀዋል።

ትራክተሮቹም በየአካባቢዎቹ እየተንቀሳቀሱ የሚያርሱ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ አርሶ አደሮቹ በተፈጠረላቸው ምቹ ሁኔታ በኑሮው እየተለወጠ መሆኑንም ተናግረዋል።

በተያዘው የበልግ ወቅት አርሶ አደሩ፣ ባለሙያውና አመራሩ ጊዜውን በአግባቡ በመጠቀም ባለው ዝናብ ዘር በመዝራትና በመንከባከብ በኩል ርብርብ ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026