አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) ከእስራኤል ኤነርጂና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ኤሊ ኮህን ጋር በሁለትዮሽና በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
ውይይቱ ሁለቱ ሀገራት በኢነርጂ፣ በማዕድን፤ በመሰረተ ልማት እና ኢንቨስትመንት ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ ነው።
ሚኒስትሮቹ ሀገራቱ በፖለቲካ እና ደህንነት ዘርፍ ያላቸውን ጠንካራ ትብብር በኢኮኖሚ ዘርፍም ይበልጥ እንዲዳብር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ካላት ሰፊ የታዳሽ ኃይል አቅም አንጻር የእስራኤል ኩባንያዎች መሰማራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ያሉ የትብብር አማራጮችን ለመቃኘት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የእስራኤል ባለሀብቶች በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ኢንቨስትመንት በሚሰማሩበት ሁኔታ እና ሀገሪቷ በመስኖ እና ግብርና ቴክኖሎጂ ያላትን የቴክኖሎጂ አቆም በመጠቀም የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ ትብብር መፍጠር እንደሚቻልም አንስተዋል።
የእስራኤል የኢነርጂ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ኢሊ ኮኸን የሀገራቸው መንግስት የእስራኤል ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያሉ የኢንቨስትመንት እድሎችን እንዲጠቀሙ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
በቅርቡም በሳቸው የተመራ የንግድ ልዑክ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ የትብብር አማራጮችን ማየት የሚችልበትን ሁኔታ እንደሚያመቻቹም አመልክተዋል።
የእስራኤል የኢነርጂ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ኢሊ ኮኸን እ.አ.አ በፊብሩዋሪ 2025 በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ሚኒስትሩ በቆይታቸው ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ኢትዮጵያ እና እስራኤል በግብርና፣ በቴክኖሎጂ፣ በጤና፣ በምርምር፣ በኢኖቬሽን እና ኤነርጂ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025