
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) ከእስራኤል ኤነርጂና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ኤሊ ኮህን ጋር በሁለትዮሽና በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
ውይይቱ ሁለቱ ሀገራት በኢነርጂ፣ በማዕድን፤ በመሰረተ ልማት እና ኢንቨስትመንት ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ ነው።
ሚኒስትሮቹ ሀገራቱ በፖለቲካ እና ደህንነት ዘርፍ ያላቸውን ጠንካራ ትብብር በኢኮኖሚ ዘርፍም ይበልጥ እንዲዳብር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ካላት ሰፊ የታዳሽ ኃይል አቅም አንጻር የእስራኤል ኩባንያዎች መሰማራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ያሉ የትብብር አማራጮችን ለመቃኘት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።

የእስራኤል ባለሀብቶች በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ኢንቨስትመንት በሚሰማሩበት ሁኔታ እና ሀገሪቷ በመስኖ እና ግብርና ቴክኖሎጂ ያላትን የቴክኖሎጂ አቆም በመጠቀም የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ ትብብር መፍጠር እንደሚቻልም አንስተዋል።
የእስራኤል የኢነርጂ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ኢሊ ኮኸን የሀገራቸው መንግስት የእስራኤል ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያሉ የኢንቨስትመንት እድሎችን እንዲጠቀሙ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
በቅርቡም በሳቸው የተመራ የንግድ ልዑክ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ የትብብር አማራጮችን ማየት የሚችልበትን ሁኔታ እንደሚያመቻቹም አመልክተዋል።
የእስራኤል የኢነርጂ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ኢሊ ኮኸን እ.አ.አ በፊብሩዋሪ 2025 በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ሚኒስትሩ በቆይታቸው ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ኢትዮጵያ እና እስራኤል በግብርና፣ በቴክኖሎጂ፣ በጤና፣ በምርምር፣ በኢኖቬሽን እና ኤነርጂ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025