ጋምቤላ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የተተገበረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት ሃብት ልማትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
መርሃ ግብሩ በክልሉ ከተጀመረ ወዲህ በርካታ የወተት፣ የንብ ማነብ፣ የዶሮና የዓሳ መንደሮች መፈጠራቸውንም ቢሮው ገልጿል።
የቢሮ ኃላፊዋ ወይዘሮ ክርሚስ ሌሮ፤ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የክልሉን የእንስሳት ልማት ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ለኢዜአ ተናግረዋል።
ይህም ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል ከመፍጠሩ ባለፈ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የዶሮ፣ የወተት፣ የንብ ማነብና የዓሳ መንደሮች እንዲፈጠሩ አስችሏልም ብለዋል።
በክልሉ ጋምቤላ ከተማ፣ ጎደሬ፣ መንጌሽና ጋምቤላ ወረዳዎች በርካታ የንብ ማነቢየ መንደሮች መፈጠራቸውን የገለጹት ኃላፊዋ፤ በኑዌር ዞን በሚገኙ አምስት ወረዳዎችና ሌሎች አካባቢዎች በርካታ የወተት መንደሮች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።
የወተት ምርቱን አዘምኖ በመጠቀምና የተሻሻሉ የወተት ላሞችን የማዳቀል ስራ ላይ ለውጦች እንዳሉም ተናግረዋል።
በክልሉ በአኝዋሃና በኑዌር ዞኖችም በስፋት የዓሳ መንደሮች መፈጠራቸውን ጠቁመው፤ ቢሮው በዘርፉ የተገኘውን ውጤት ይበልጥ ለማጠናከር የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።
በክልሉ በዶሮ እርባታ ዘርፍ ከተሰማሩት መካከል አቶ ወንድሙ ባልቻ በሰጡት አስተያየት፤ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የፈጠረውን ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም በዘርፉ በመሰማራታቸው ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ በዘርፉ ለመሰማራት ከፍተኛ መነቃቃት እንደፈጠረላቸው የገለጹት ደግሞ በጎደሬ ወረዳ በንብ ማነብ ስራ ላይ የተሰማሩት አርሶ አደር ብራሃኑ ገዳሙ ናቸው።
መንግስት ዘርፉን ለማሳደግ የግብዓት አቅርቦት በማመቻቸቱ የ72 ባህላዊና ዘመናዊ ቀፎዎች ባለቤት መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025