የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በጋምቤላ ክልል የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት ሃብት ልማትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው

Mar 15, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የተተገበረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት ሃብት ልማትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

መርሃ ግብሩ በክልሉ ከተጀመረ ወዲህ በርካታ የወተት፣ የንብ ማነብ፣ የዶሮና የዓሳ መንደሮች መፈጠራቸውንም ቢሮው ገልጿል።

የቢሮ ኃላፊዋ ወይዘሮ ክርሚስ ሌሮ፤ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የክልሉን የእንስሳት ልማት ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ለኢዜአ ተናግረዋል።

ይህም ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል ከመፍጠሩ ባለፈ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የዶሮ፣ የወተት፣ የንብ ማነብና የዓሳ መንደሮች እንዲፈጠሩ አስችሏልም ብለዋል።

በክልሉ ጋምቤላ ከተማ፣ ጎደሬ፣ መንጌሽና ጋምቤላ ወረዳዎች በርካታ የንብ ማነቢየ መንደሮች መፈጠራቸውን የገለጹት ኃላፊዋ፤ በኑዌር ዞን በሚገኙ አምስት ወረዳዎችና ሌሎች አካባቢዎች በርካታ የወተት መንደሮች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።

የወተት ምርቱን አዘምኖ በመጠቀምና የተሻሻሉ የወተት ላሞችን የማዳቀል ስራ ላይ ለውጦች እንዳሉም ተናግረዋል።

በክልሉ በአኝዋሃና በኑዌር ዞኖችም በስፋት የዓሳ መንደሮች መፈጠራቸውን ጠቁመው፤ ቢሮው በዘርፉ የተገኘውን ውጤት ይበልጥ ለማጠናከር የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።

በክልሉ በዶሮ እርባታ ዘርፍ ከተሰማሩት መካከል አቶ ወንድሙ ባልቻ በሰጡት አስተያየት፤ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የፈጠረውን ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም በዘርፉ በመሰማራታቸው ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ በዘርፉ ለመሰማራት ከፍተኛ መነቃቃት እንደፈጠረላቸው የገለጹት ደግሞ በጎደሬ ወረዳ በንብ ማነብ ስራ ላይ የተሰማሩት አርሶ አደር ብራሃኑ ገዳሙ ናቸው።

መንግስት ዘርፉን ለማሳደግ የግብዓት አቅርቦት በማመቻቸቱ የ72 ባህላዊና ዘመናዊ ቀፎዎች ባለቤት መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025