
ጋምቤላ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የተተገበረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት ሃብት ልማትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
መርሃ ግብሩ በክልሉ ከተጀመረ ወዲህ በርካታ የወተት፣ የንብ ማነብ፣ የዶሮና የዓሳ መንደሮች መፈጠራቸውንም ቢሮው ገልጿል።
የቢሮ ኃላፊዋ ወይዘሮ ክርሚስ ሌሮ፤ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የክልሉን የእንስሳት ልማት ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ለኢዜአ ተናግረዋል።
ይህም ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል ከመፍጠሩ ባለፈ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የዶሮ፣ የወተት፣ የንብ ማነብና የዓሳ መንደሮች እንዲፈጠሩ አስችሏልም ብለዋል።
በክልሉ ጋምቤላ ከተማ፣ ጎደሬ፣ መንጌሽና ጋምቤላ ወረዳዎች በርካታ የንብ ማነቢየ መንደሮች መፈጠራቸውን የገለጹት ኃላፊዋ፤ በኑዌር ዞን በሚገኙ አምስት ወረዳዎችና ሌሎች አካባቢዎች በርካታ የወተት መንደሮች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።
የወተት ምርቱን አዘምኖ በመጠቀምና የተሻሻሉ የወተት ላሞችን የማዳቀል ስራ ላይ ለውጦች እንዳሉም ተናግረዋል።
በክልሉ በአኝዋሃና በኑዌር ዞኖችም በስፋት የዓሳ መንደሮች መፈጠራቸውን ጠቁመው፤ ቢሮው በዘርፉ የተገኘውን ውጤት ይበልጥ ለማጠናከር የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።
በክልሉ በዶሮ እርባታ ዘርፍ ከተሰማሩት መካከል አቶ ወንድሙ ባልቻ በሰጡት አስተያየት፤ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የፈጠረውን ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም በዘርፉ በመሰማራታቸው ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ በዘርፉ ለመሰማራት ከፍተኛ መነቃቃት እንደፈጠረላቸው የገለጹት ደግሞ በጎደሬ ወረዳ በንብ ማነብ ስራ ላይ የተሰማሩት አርሶ አደር ብራሃኑ ገዳሙ ናቸው።
መንግስት ዘርፉን ለማሳደግ የግብዓት አቅርቦት በማመቻቸቱ የ72 ባህላዊና ዘመናዊ ቀፎዎች ባለቤት መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026