
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 06/2017(ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መሪዎች ለቀጣናው ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ በመተማመን ላይ የተመሰረተ ትብብር ማጠናከር እንደሚገባቸው ኢዜአ ያነጋገራቸው የቀጣናው ሀገራት ጋዜጠኞች ገለጹ።
ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ጋዜጠኞች በቀጣናዊ ሰላም፣ ልማትና ትስስር ዙሪያ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ስቱዲዮ ተወያይተዋል።
ጋዜጠኞቹ በውይይታቸው የቀጣናው ሀገራት መሪዎች በሀገራዊና እና ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን በመተማመን ላይ የተመሰረተ ትብብር ማጠናከር እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡
ኬንያዊ ጋዜጠኛ ናሊስተን ጃጊ ተለዋዋጭ በሆነው የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላምና ፀጥታ ሁኔታ "ለአፍሪካዊ ችግር፣ አፍሪካዊ መፍትሄ” በሚለው መርህ መሰረት ለዘላቂ ሰላም መተባበር ይገባል ብሏል።

የደቡብ ሱዳን ጋዜጠኛው ኦባንጅ ኦከች ለቀጣናዊ ችግሮችን ጎረቤት ሀገራት ከማንም በተሻለ በቅርበት መምከርና ለችግሩ እልባት መስጠት እንጂ ሶስተኛ ሩቅ ወገን መጋበዝና ጉዳዩን ማባባስ እንደማይገባቸው ነው ያነሳው።

ኡጋንዳዊት ጋዜጠኛ ዲያና አኩሎ በበኩሉ ሰላምን ለማረጋገጥ ሚዲያ ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቅሶ፤ ጋዜጠኞች ግጭትን አባባሽ ሳይሆን ለቀጣናዊ ሰላምና አብሮነት አበክረው እንዲሰሩ ጠይቃለች።

የተዛቡ እና የተሳሳቱ መረጃዎች ትልቅ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ እየፈጠሩ ባሉበት ወቅት ትክክለኛውን መረጃ በወቅቱ ማድረስ አስፈላጊ ስለመሆኑ ተናግራለች፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025