የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ የመሪዎችን መተማመንና ብርቱ ትብብር ይጠይቃል- የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ጋዜጠኞች

Mar 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 06/2017(ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መሪዎች ለቀጣናው ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ በመተማመን ላይ የተመሰረተ ትብብር ማጠናከር እንደሚገባቸው ኢዜአ ያነጋገራቸው የቀጣናው ሀገራት ጋዜጠኞች ገለጹ።

ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ጋዜጠኞች በቀጣናዊ ሰላም፣ ልማትና ትስስር ዙሪያ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ስቱዲዮ ተወያይተዋል።

ጋዜጠኞቹ በውይይታቸው የቀጣናው ሀገራት መሪዎች በሀገራዊና እና ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን በመተማመን ላይ የተመሰረተ ትብብር ማጠናከር እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡

ኬንያዊ ጋዜጠኛ ናሊስተን ጃጊ ተለዋዋጭ በሆነው የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላምና ፀጥታ ሁኔታ "ለአፍሪካዊ ችግር፣ አፍሪካዊ መፍትሄ” በሚለው መርህ መሰረት ለዘላቂ ሰላም መተባበር ይገባል ብሏል።


የደቡብ ሱዳን ጋዜጠኛው ኦባንጅ ኦከች ለቀጣናዊ ችግሮችን ጎረቤት ሀገራት ከማንም በተሻለ በቅርበት መምከርና ለችግሩ እልባት መስጠት እንጂ ሶስተኛ ሩቅ ወገን መጋበዝና ጉዳዩን ማባባስ እንደማይገባቸው ነው ያነሳው።


ኡጋንዳዊት ጋዜጠኛ ዲያና አኩሎ በበኩሉ ሰላምን ለማረጋገጥ ሚዲያ ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቅሶ፤ ጋዜጠኞች ግጭትን አባባሽ ሳይሆን ለቀጣናዊ ሰላምና አብሮነት አበክረው እንዲሰሩ ጠይቃለች።


የተዛቡ እና የተሳሳቱ መረጃዎች ትልቅ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ እየፈጠሩ ባሉበት ወቅት ትክክለኛውን መረጃ በወቅቱ ማድረስ አስፈላጊ ስለመሆኑ ተናግራለች፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026