
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 06/2017(ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መሪዎች ለቀጣናው ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ በመተማመን ላይ የተመሰረተ ትብብር ማጠናከር እንደሚገባቸው ኢዜአ ያነጋገራቸው የቀጣናው ሀገራት ጋዜጠኞች ገለጹ።
ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ጋዜጠኞች በቀጣናዊ ሰላም፣ ልማትና ትስስር ዙሪያ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ስቱዲዮ ተወያይተዋል።
ጋዜጠኞቹ በውይይታቸው የቀጣናው ሀገራት መሪዎች በሀገራዊና እና ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን በመተማመን ላይ የተመሰረተ ትብብር ማጠናከር እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡
ኬንያዊ ጋዜጠኛ ናሊስተን ጃጊ ተለዋዋጭ በሆነው የምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ሰላምና ፀጥታ ሁኔታ "ለአፍሪካዊ ችግር፣ አፍሪካዊ መፍትሄ” በሚለው መርህ መሰረት ለዘላቂ ሰላም መተባበር ይገባል ብሏል።

የደቡብ ሱዳን ጋዜጠኛው ኦባንጅ ኦከች ለቀጣናዊ ችግሮችን ጎረቤት ሀገራት ከማንም በተሻለ በቅርበት መምከርና ለችግሩ እልባት መስጠት እንጂ ሶስተኛ ሩቅ ወገን መጋበዝና ጉዳዩን ማባባስ እንደማይገባቸው ነው ያነሳው።

ኡጋንዳዊት ጋዜጠኛ ዲያና አኩሎ በበኩሉ ሰላምን ለማረጋገጥ ሚዲያ ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቅሶ፤ ጋዜጠኞች ግጭትን አባባሽ ሳይሆን ለቀጣናዊ ሰላምና አብሮነት አበክረው እንዲሰሩ ጠይቃለች።

የተዛቡ እና የተሳሳቱ መረጃዎች ትልቅ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ እየፈጠሩ ባሉበት ወቅት ትክክለኛውን መረጃ በወቅቱ ማድረስ አስፈላጊ ስለመሆኑ ተናግራለች፡፡
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026