ጅማ፣መጋቢት 7/2017(ኢዜአ) ፡-በጅማ ከተማ የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና በ“ኦንላይን” ለተከታተሉ 842 ሰዎች ዛሬ የምስክር ወረቀት ተሰጠ።
የምስክር ወረቀቱ የተሰጣቸው መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ወጣቶችና ሌሎችም የሕብረተሰብ ክፍሎች ናቸው ።
የኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ስልጠና ዌብ ፕሮግራሚንግ፣ አንድሮይድ ማበልፀግ፣ የዳታ አናላይስስ እና የአርቴፊሻል ኢንተለጄንስ መሰረታዊ ክህሎት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
ይህም በተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና በኢትዮጵያ መንግስት የሚተገበር ሲሆን፤ሐምሌ 16 /2016 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በይፋ መጀመሩ ይታወሳል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያንን ለመድረስ ታቅዶ በተጀመረው የ”ኦንላይን” ስልጠና መረሃ ግብር የዲጂታል ማህበረሰብን በመፍጠር አሰራርንና አገልግሎትን ለማሳለጥ እንደሚያግዝ ተመልክቷል።
በጅማ ከተማ በ“ኦንላይን” ስልጠናውን ተከታትላው ዛሬ የምስክር ወረቀት የተሰጣቸው ወጣቶችና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች የዚሁ መረሃ ግብር አካል ናቸው።
በመረሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ግርማ ባይሳ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተቀረጸው የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ፕሮግራም የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ ነው ብለዋል።
የመማር ማስተማር ሂደትን ለማቀላጠፍና የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት የሚያግዝ መሆኑን አመልክተው፥ እድሉን በአግባቡ መጠቀም አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
በኦሮሚያ ክልል የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና በ”ኦንላይን” ለመስጠት ከታቀደው ውስጥ እስካሁን ለ500ሺህ ሰዎች መሰጠቱን ጠቁመዋል።
የጅማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በበኩላቸው፥በጅማ ከተማ የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና ተከታትለው ዛሬ የምስክር ወረቀት የተሰጣቸው መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ወጣቶችና ሌሎችም የሕብረተሰብ ክፍሎች መሆናቸውን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያውያን ኮደርስ በዲጂታል የተደገፈ የአሰራር ስርዓትን ለመፍጠር ታስቦ የተቀረጸ መሆኑን አንስተዋል።
ከሰልጣኞቹ መካከል የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መምህር ብርሃኑ መንግስቱ በሰጡት አስተያየት፥ አንድሮይድ ማበልፀግ እና የዳታ አናላይስስ ስልጠና ወስጄ እውቀት አግኝቼበታለው ብለዋል።
የኮሚኒቲ ስኩል ተማሪ ቀነኒ ታደሰ በበኩሉ፤ የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠናው ከዲጂታል ዓለም ጋር በመተዋወቅ በቴክኖሎጂው ተጠቃሚ ለመሆን ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረለት ገልጿል።
በጅማ ከተማ በተመሳሳይ ስልጠናውን የሚከታተሉ ሌሎችም ሰዎች በሂደት ላይ እንደሚገኙ ተመልክቷል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025