የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በጅማ ከተማ የኮደርስ ስልጠና ለተከታተሉ 842 ሰዎች የምስክር ወረቀት ተሰጠ

Mar 17, 2025

IDOPRESS

ጅማ፣መጋቢት 7/2017(ኢዜአ) ፡-በጅማ ከተማ የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና በ“ኦንላይን” ለተከታተሉ 842 ሰዎች ዛሬ የምስክር ወረቀት ተሰጠ።


የምስክር ወረቀቱ የተሰጣቸው መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ወጣቶችና ሌሎችም የሕብረተሰብ ክፍሎች ናቸው ።


የኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ስልጠና ዌብ ፕሮግራሚንግ፣ አንድሮይድ ማበልፀግ፣ የዳታ አናላይስስ እና የአርቴፊሻል ኢንተለጄንስ መሰረታዊ ክህሎት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።


ይህም በተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና በኢትዮጵያ መንግስት የሚተገበር ሲሆን፤ሐምሌ 16 /2016 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በይፋ መጀመሩ ይታወሳል።


በሀገር አቀፍ ደረጃ አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያንን ለመድረስ ታቅዶ በተጀመረው የ”ኦንላይን” ስልጠና መረሃ ግብር የዲጂታል ማህበረሰብን በመፍጠር አሰራርንና አገልግሎትን ለማሳለጥ እንደሚያግዝ ተመልክቷል።


በጅማ ከተማ በ“ኦንላይን” ስልጠናውን ተከታትላው ዛሬ የምስክር ወረቀት የተሰጣቸው ወጣቶችና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች የዚሁ መረሃ ግብር አካል ናቸው።


በመረሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ግርማ ባይሳ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተቀረጸው የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ፕሮግራም የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ ነው ብለዋል።


የመማር ማስተማር ሂደትን ለማቀላጠፍና የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት የሚያግዝ መሆኑን አመልክተው፥ እድሉን በአግባቡ መጠቀም አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።


በኦሮሚያ ክልል የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና በ”ኦንላይን” ለመስጠት ከታቀደው ውስጥ እስካሁን ለ500ሺህ ሰዎች መሰጠቱን ጠቁመዋል።


የጅማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በበኩላቸው፥በጅማ ከተማ የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና ተከታትለው ዛሬ የምስክር ወረቀት የተሰጣቸው መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ወጣቶችና ሌሎችም የሕብረተሰብ ክፍሎች መሆናቸውን ተናግረዋል።


የኢትዮጵያውያን ኮደርስ በዲጂታል የተደገፈ የአሰራር ስርዓትን ለመፍጠር ታስቦ የተቀረጸ መሆኑን አንስተዋል።


ከሰልጣኞቹ መካከል የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መምህር ብርሃኑ መንግስቱ በሰጡት አስተያየት፥ አንድሮይድ ማበልፀግ እና የዳታ አናላይስስ ስልጠና ወስጄ እውቀት አግኝቼበታለው ብለዋል።


የኮሚኒቲ ስኩል ተማሪ ቀነኒ ታደሰ በበኩሉ፤ የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠናው ከዲጂታል ዓለም ጋር በመተዋወቅ በቴክኖሎጂው ተጠቃሚ ለመሆን ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረለት ገልጿል።


በጅማ ከተማ በተመሳሳይ ስልጠናውን የሚከታተሉ ሌሎችም ሰዎች በሂደት ላይ እንደሚገኙ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025