የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በጅማ ከተማ የኮደርስ ስልጠና ለተከታተሉ 842 ሰዎች የምስክር ወረቀት ተሰጠ

Mar 17, 2025

IDOPRESS

ጅማ፣መጋቢት 7/2017(ኢዜአ) ፡-በጅማ ከተማ የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና በ“ኦንላይን” ለተከታተሉ 842 ሰዎች ዛሬ የምስክር ወረቀት ተሰጠ።


የምስክር ወረቀቱ የተሰጣቸው መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ወጣቶችና ሌሎችም የሕብረተሰብ ክፍሎች ናቸው ።


የኢትዮጵያዊያን ኮደርስ ስልጠና ዌብ ፕሮግራሚንግ፣ አንድሮይድ ማበልፀግ፣ የዳታ አናላይስስ እና የአርቴፊሻል ኢንተለጄንስ መሰረታዊ ክህሎት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።


ይህም በተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና በኢትዮጵያ መንግስት የሚተገበር ሲሆን፤ሐምሌ 16 /2016 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በይፋ መጀመሩ ይታወሳል።


በሀገር አቀፍ ደረጃ አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያንን ለመድረስ ታቅዶ በተጀመረው የ”ኦንላይን” ስልጠና መረሃ ግብር የዲጂታል ማህበረሰብን በመፍጠር አሰራርንና አገልግሎትን ለማሳለጥ እንደሚያግዝ ተመልክቷል።


በጅማ ከተማ በ“ኦንላይን” ስልጠናውን ተከታትላው ዛሬ የምስክር ወረቀት የተሰጣቸው ወጣቶችና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች የዚሁ መረሃ ግብር አካል ናቸው።


በመረሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ግርማ ባይሳ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተቀረጸው የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ፕሮግራም የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ ነው ብለዋል።


የመማር ማስተማር ሂደትን ለማቀላጠፍና የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት የሚያግዝ መሆኑን አመልክተው፥ እድሉን በአግባቡ መጠቀም አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።


በኦሮሚያ ክልል የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና በ”ኦንላይን” ለመስጠት ከታቀደው ውስጥ እስካሁን ለ500ሺህ ሰዎች መሰጠቱን ጠቁመዋል።


የጅማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በበኩላቸው፥በጅማ ከተማ የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና ተከታትለው ዛሬ የምስክር ወረቀት የተሰጣቸው መምህራንና ተማሪዎችን ጨምሮ ወጣቶችና ሌሎችም የሕብረተሰብ ክፍሎች መሆናቸውን ተናግረዋል።


የኢትዮጵያውያን ኮደርስ በዲጂታል የተደገፈ የአሰራር ስርዓትን ለመፍጠር ታስቦ የተቀረጸ መሆኑን አንስተዋል።


ከሰልጣኞቹ መካከል የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መምህር ብርሃኑ መንግስቱ በሰጡት አስተያየት፥ አንድሮይድ ማበልፀግ እና የዳታ አናላይስስ ስልጠና ወስጄ እውቀት አግኝቼበታለው ብለዋል።


የኮሚኒቲ ስኩል ተማሪ ቀነኒ ታደሰ በበኩሉ፤ የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠናው ከዲጂታል ዓለም ጋር በመተዋወቅ በቴክኖሎጂው ተጠቃሚ ለመሆን ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረለት ገልጿል።


በጅማ ከተማ በተመሳሳይ ስልጠናውን የሚከታተሉ ሌሎችም ሰዎች በሂደት ላይ እንደሚገኙ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026