የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የባህር ዳር ከተማ ገና ብዙ መገለጥ የሚችሉ ውበቶችን በተፈጥሮ የታደለች ማራኪ ከተማ ነች-ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)

Mar 17, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤መጋቢት 7/2017 (ኢዜአ)፦በባህርዳር ከተማ እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት ከተማዋ ገና ብዙ መገለጥ የሚችሉ ውበቶችን በተፈጥሮ የታደለች ሳቢና ማራኪ ከተማ መሆኗን ያሳዩ ናቸው ሲሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።


በባህር ዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች በፌዴራልና በክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ዛሬ ተጎብኝተዋል።


ሚኒስትሩ ከጉብኝቱ በኋላ በሰጡት አስተያየት እንዳሉት፥ ባህር ዳር ገና ብዙ መገለጥ የሚችሉ ውበቶችን በተፈጥሮ የታደለች ሳቢና ማራኪ ከተማ ነች።


ከተማዋ በከፍተኛ የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ የምትገኝ መሆኗን ገልፀው፥ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው እንደተመለከቱም ተናግረዋል።


ይህም የከተማዋ ውበት ይበልጥ እንዲገለጥ ከማድረግ ባለፈ ከጣና ኃይቅ ጋር የሚያገናኙ መንገዶች በ7 ቦታዎች ተከፍተው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ገልፀዋል።


ይህም ለከተማዋ ነዋሪዎችም ሆነ ለጎብኚዎች ጣናን በቀላሉ የሚያይበትን ዕድል እንዲፈጠር ማድረጉንም አመልክተዋል።


እንዲሁም በከተማዋ የሚገኙ ህንፃዎች እየታደሱና ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትን የሚያጎናፅፍ የቀለም ኮድ እየተተገበረ መሆኑ ለከተማዋ ተደማሪ ውበትና ድምቀት ማላበሱንም አስረድተዋል።


የተጀመረው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ውበት አጉልቶ በማውጣት ዓለም አቀፍ የቱሪዝም መዳረሻነቷን ለማሳደግ በቀጣይም ስራው ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አሳስበዋል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የክልሉ የከተሞችና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ በ ''8 ሪጂዮ ፖሊታን'' ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራዎች ሌት ተቀን እየተከናወኑ ነው።


የኮሪደር ልማቱ የስራ ባህልን ከመቀየሩም በላይ በተለይ በጣና ዳርቻ የተከፈቱ ቦታዎች ነዋሪዎችና ከሌላ ቦታ የመጡ እንግዶች ያለምንም ስጋት እየተዝናኑ እንዲጎበኙ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩን ተናግረዋል።


የኮሪደር ልማቱ ይዞት የመጣው መልካም ነገር ያሉንን ሃብቶችና ፀጋዎች በአግባቡ አልምተን በመጠቀም የከተሞችን እድገት እንድናፋጥን አድርጓል ብለዋል።


በቀጣይም የከተሞችን ልማትና ዕድገት ለማፋጠን የኮሪደርና ሌሎች ተያያዥ ስራዎች በጥራትና በፍጥነት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።


የኢንፎርሜሽንና መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዮዳሄ አርዓያስላሴ በበኩላቸው፥ ለባህር ዳር ከተማ የውበት መገለጫ ከሆኑ ዘንባባዎቿ ጋር የሚያምር የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን መታዘባቸውን ገልጸዋል።


የተረጋጋ ሰላም በከተማዋ በመኖሩም በርካታ የህብረተሰብ ክፍል በኮሪደር ልማቱ በጣና ዳርቻ በተከፈቱ መንገዶች ከነቤተሰባቸው እየተዝናኑ መሆኑን ተመልክተዋል።


በዚህ ወቅት ወደ ባህር ዳር መጥቶ ኢንቨስት የሚያደርግ ባለሃብት በቀጣይ ያማረ ፍሬን ይበላል ያሉት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ከተማዋ ለዚህ የተመቸች ውብና ማራኪ መሆኗን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026