የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የባህር ዳር ከተማ ገና ብዙ መገለጥ የሚችሉ ውበቶችን በተፈጥሮ የታደለች ማራኪ ከተማ ነች-ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)

Mar 17, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤መጋቢት 7/2017 (ኢዜአ)፦በባህርዳር ከተማ እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት ከተማዋ ገና ብዙ መገለጥ የሚችሉ ውበቶችን በተፈጥሮ የታደለች ሳቢና ማራኪ ከተማ መሆኗን ያሳዩ ናቸው ሲሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።


በባህር ዳር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች በፌዴራልና በክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ዛሬ ተጎብኝተዋል።


ሚኒስትሩ ከጉብኝቱ በኋላ በሰጡት አስተያየት እንዳሉት፥ ባህር ዳር ገና ብዙ መገለጥ የሚችሉ ውበቶችን በተፈጥሮ የታደለች ሳቢና ማራኪ ከተማ ነች።


ከተማዋ በከፍተኛ የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ የምትገኝ መሆኗን ገልፀው፥ እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደርና ሌሎች የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው እንደተመለከቱም ተናግረዋል።


ይህም የከተማዋ ውበት ይበልጥ እንዲገለጥ ከማድረግ ባለፈ ከጣና ኃይቅ ጋር የሚያገናኙ መንገዶች በ7 ቦታዎች ተከፍተው ለአገልግሎት መብቃታቸውን ገልፀዋል።


ይህም ለከተማዋ ነዋሪዎችም ሆነ ለጎብኚዎች ጣናን በቀላሉ የሚያይበትን ዕድል እንዲፈጠር ማድረጉንም አመልክተዋል።


እንዲሁም በከተማዋ የሚገኙ ህንፃዎች እየታደሱና ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትን የሚያጎናፅፍ የቀለም ኮድ እየተተገበረ መሆኑ ለከተማዋ ተደማሪ ውበትና ድምቀት ማላበሱንም አስረድተዋል።


የተጀመረው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ውበት አጉልቶ በማውጣት ዓለም አቀፍ የቱሪዝም መዳረሻነቷን ለማሳደግ በቀጣይም ስራው ይበልጥ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አሳስበዋል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የክልሉ የከተሞችና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) እንዳሉት በክልሉ በ ''8 ሪጂዮ ፖሊታን'' ከተሞች የኮሪደር ልማት ስራዎች ሌት ተቀን እየተከናወኑ ነው።


የኮሪደር ልማቱ የስራ ባህልን ከመቀየሩም በላይ በተለይ በጣና ዳርቻ የተከፈቱ ቦታዎች ነዋሪዎችና ከሌላ ቦታ የመጡ እንግዶች ያለምንም ስጋት እየተዝናኑ እንዲጎበኙ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩን ተናግረዋል።


የኮሪደር ልማቱ ይዞት የመጣው መልካም ነገር ያሉንን ሃብቶችና ፀጋዎች በአግባቡ አልምተን በመጠቀም የከተሞችን እድገት እንድናፋጥን አድርጓል ብለዋል።


በቀጣይም የከተሞችን ልማትና ዕድገት ለማፋጠን የኮሪደርና ሌሎች ተያያዥ ስራዎች በጥራትና በፍጥነት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።


የኢንፎርሜሽንና መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዮዳሄ አርዓያስላሴ በበኩላቸው፥ ለባህር ዳር ከተማ የውበት መገለጫ ከሆኑ ዘንባባዎቿ ጋር የሚያምር የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን መታዘባቸውን ገልጸዋል።


የተረጋጋ ሰላም በከተማዋ በመኖሩም በርካታ የህብረተሰብ ክፍል በኮሪደር ልማቱ በጣና ዳርቻ በተከፈቱ መንገዶች ከነቤተሰባቸው እየተዝናኑ መሆኑን ተመልክተዋል።


በዚህ ወቅት ወደ ባህር ዳር መጥቶ ኢንቨስት የሚያደርግ ባለሃብት በቀጣይ ያማረ ፍሬን ይበላል ያሉት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ከተማዋ ለዚህ የተመቸች ውብና ማራኪ መሆኗን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026