የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የጥንቃቄ መልዕክት! ከአጭበርባሪዎች እንዴት ራሳችንን እንጠብቅ?

Mar 18, 2025

IDOPRESS


አጭበርባሪዎች ኢላማ ያደረጓቸውን አካላት ለማጭበርበር የሚጠቀሙባቸው የተለያዩ መንገዶች ቢኖሩም በስፋት ከተለመዱት የማጭበርበሪያ መንገዶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦


👉በአጭር የጽሁፍ መልዕክት፦ አጭበርባሪዎች ቤተሰብ፣ ከጓደኛ፣ ከቢዝነስ አጋር ወይም ከመንግስት መስሪያ ቤት የተላከ በማስመሰል በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ያጭበረብራሉ።


👉በስልክ ጥሪ፦ ከሶስት ማጭበርበሮች መካከል አንዱ በስልክ ጥሪ የሚከሰት መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ። አጭበርባሪዎች ጥሪዎችን ከባንክ፣ ከቴሌኮም አቅራቢዎች፣ ከህግ አስከባሪዎችና መሰል ተቋማት የደወሉ በማስመሰል ለማታለል ይሞክራሉ።


👉በኢ-ሜይል፦ ከአጭበርባሪዎች የተላኩ ኢሜይሎች እውነተኛ ይመስላሉ፣ ነገር ግን በደንብ ሲመረመሩ ገንዘብዎን ወይም መረጃዎን ለመስረቅ የተነደፉ አደገኛ ሊንኮችና አባሪዎችን ይሆናሉ። በባህሪያቸው አስቸኳይ የሚሉና ከመንግስት ወይም ከህግ አስከባሪ ተቋማት የተላኩ መስለው ይላካሉ።


👉በማህበራዊ ሚዲያ፦ የማህበራዊ ሚዲያዎች ለአጭበርባሪዎች የተመቹ ናቸው። አጭበርባሪዎች ሃሰተኛ አካውንቶችንና ፕሮፋይል በመለጠፍ ጓደኛ፣ ወዳጅና የቅርብ ሰው በመምሰል ያጭበረብራሉ።


👉በድረገጽ፦ አጭበርባሪዎች የታወቁ ካምፓኒዎች ለመምሰል ሃሰተኛ ድረገጾችን ይፈጥራሉ። ከዚህ ባሻገር ታዋቂ ሰዎችን ምስክርነት እንደሰጡ በማስመሰል ለማታለል የሚሞክሩ ሲሆን እርስዎ በድረገጾቹ ላይ እምነት እንዲጥሉ ሃሰተኛ ሪቪው ያስቀምጣሉ።


👉በአካል፦ አንዳንድ ማጭበርበሮች በአካል ይፈጸማሉ። ቤት ለቤት፣ እየተዝናኑ ወይም ታክሲ እየጠበቁ፣ በአደባባዮችና በተለያዩ ቦታዎች ወደ እርስዎ ቀረብ ብለው ለአንድ ‘የበጎ አድራጎት ድርጅት’ መዋጮ እየሰበሰቡ በመምሰል መዋጮ ሊጠይቁዎ ይችላሉ። ከዚህ ባለፈ ግላዊ መረጃዎችዎን ለማግኘት እንዲረዳቸው የዳሰሳ ጥናት እየሰሩ በማስመሰል ፎርም በማስሞላት መረጃዎችን በመመንተፍ ሊያጭበረብሩ ይችላሉ።


የጥንቃቄ መልዕክቶቹ መረጃ የተገኘው ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026