የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የጥንቃቄ መልዕክት! ከአጭበርባሪዎች እንዴት ራሳችንን እንጠብቅ?

Mar 18, 2025

IDOPRESS


አጭበርባሪዎች ኢላማ ያደረጓቸውን አካላት ለማጭበርበር የሚጠቀሙባቸው የተለያዩ መንገዶች ቢኖሩም በስፋት ከተለመዱት የማጭበርበሪያ መንገዶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦


👉በአጭር የጽሁፍ መልዕክት፦ አጭበርባሪዎች ቤተሰብ፣ ከጓደኛ፣ ከቢዝነስ አጋር ወይም ከመንግስት መስሪያ ቤት የተላከ በማስመሰል በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ያጭበረብራሉ።


👉በስልክ ጥሪ፦ ከሶስት ማጭበርበሮች መካከል አንዱ በስልክ ጥሪ የሚከሰት መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ። አጭበርባሪዎች ጥሪዎችን ከባንክ፣ ከቴሌኮም አቅራቢዎች፣ ከህግ አስከባሪዎችና መሰል ተቋማት የደወሉ በማስመሰል ለማታለል ይሞክራሉ።


👉በኢ-ሜይል፦ ከአጭበርባሪዎች የተላኩ ኢሜይሎች እውነተኛ ይመስላሉ፣ ነገር ግን በደንብ ሲመረመሩ ገንዘብዎን ወይም መረጃዎን ለመስረቅ የተነደፉ አደገኛ ሊንኮችና አባሪዎችን ይሆናሉ። በባህሪያቸው አስቸኳይ የሚሉና ከመንግስት ወይም ከህግ አስከባሪ ተቋማት የተላኩ መስለው ይላካሉ።


👉በማህበራዊ ሚዲያ፦ የማህበራዊ ሚዲያዎች ለአጭበርባሪዎች የተመቹ ናቸው። አጭበርባሪዎች ሃሰተኛ አካውንቶችንና ፕሮፋይል በመለጠፍ ጓደኛ፣ ወዳጅና የቅርብ ሰው በመምሰል ያጭበረብራሉ።


👉በድረገጽ፦ አጭበርባሪዎች የታወቁ ካምፓኒዎች ለመምሰል ሃሰተኛ ድረገጾችን ይፈጥራሉ። ከዚህ ባሻገር ታዋቂ ሰዎችን ምስክርነት እንደሰጡ በማስመሰል ለማታለል የሚሞክሩ ሲሆን እርስዎ በድረገጾቹ ላይ እምነት እንዲጥሉ ሃሰተኛ ሪቪው ያስቀምጣሉ።


👉በአካል፦ አንዳንድ ማጭበርበሮች በአካል ይፈጸማሉ። ቤት ለቤት፣ እየተዝናኑ ወይም ታክሲ እየጠበቁ፣ በአደባባዮችና በተለያዩ ቦታዎች ወደ እርስዎ ቀረብ ብለው ለአንድ ‘የበጎ አድራጎት ድርጅት’ መዋጮ እየሰበሰቡ በመምሰል መዋጮ ሊጠይቁዎ ይችላሉ። ከዚህ ባለፈ ግላዊ መረጃዎችዎን ለማግኘት እንዲረዳቸው የዳሰሳ ጥናት እየሰሩ በማስመሰል ፎርም በማስሞላት መረጃዎችን በመመንተፍ ሊያጭበረብሩ ይችላሉ።


የጥንቃቄ መልዕክቶቹ መረጃ የተገኘው ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026