የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የጥንቃቄ መልዕክት! ከአጭበርባሪዎች እንዴት ራሳችንን እንጠብቅ?

Mar 18, 2025

IDOPRESS


አጭበርባሪዎች ኢላማ ያደረጓቸውን አካላት ለማጭበርበር የሚጠቀሙባቸው የተለያዩ መንገዶች ቢኖሩም በስፋት ከተለመዱት የማጭበርበሪያ መንገዶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦


👉በአጭር የጽሁፍ መልዕክት፦ አጭበርባሪዎች ቤተሰብ፣ ከጓደኛ፣ ከቢዝነስ አጋር ወይም ከመንግስት መስሪያ ቤት የተላከ በማስመሰል በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ያጭበረብራሉ።


👉በስልክ ጥሪ፦ ከሶስት ማጭበርበሮች መካከል አንዱ በስልክ ጥሪ የሚከሰት መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ። አጭበርባሪዎች ጥሪዎችን ከባንክ፣ ከቴሌኮም አቅራቢዎች፣ ከህግ አስከባሪዎችና መሰል ተቋማት የደወሉ በማስመሰል ለማታለል ይሞክራሉ።


👉በኢ-ሜይል፦ ከአጭበርባሪዎች የተላኩ ኢሜይሎች እውነተኛ ይመስላሉ፣ ነገር ግን በደንብ ሲመረመሩ ገንዘብዎን ወይም መረጃዎን ለመስረቅ የተነደፉ አደገኛ ሊንኮችና አባሪዎችን ይሆናሉ። በባህሪያቸው አስቸኳይ የሚሉና ከመንግስት ወይም ከህግ አስከባሪ ተቋማት የተላኩ መስለው ይላካሉ።


👉በማህበራዊ ሚዲያ፦ የማህበራዊ ሚዲያዎች ለአጭበርባሪዎች የተመቹ ናቸው። አጭበርባሪዎች ሃሰተኛ አካውንቶችንና ፕሮፋይል በመለጠፍ ጓደኛ፣ ወዳጅና የቅርብ ሰው በመምሰል ያጭበረብራሉ።


👉በድረገጽ፦ አጭበርባሪዎች የታወቁ ካምፓኒዎች ለመምሰል ሃሰተኛ ድረገጾችን ይፈጥራሉ። ከዚህ ባሻገር ታዋቂ ሰዎችን ምስክርነት እንደሰጡ በማስመሰል ለማታለል የሚሞክሩ ሲሆን እርስዎ በድረገጾቹ ላይ እምነት እንዲጥሉ ሃሰተኛ ሪቪው ያስቀምጣሉ።


👉በአካል፦ አንዳንድ ማጭበርበሮች በአካል ይፈጸማሉ። ቤት ለቤት፣ እየተዝናኑ ወይም ታክሲ እየጠበቁ፣ በአደባባዮችና በተለያዩ ቦታዎች ወደ እርስዎ ቀረብ ብለው ለአንድ ‘የበጎ አድራጎት ድርጅት’ መዋጮ እየሰበሰቡ በመምሰል መዋጮ ሊጠይቁዎ ይችላሉ። ከዚህ ባለፈ ግላዊ መረጃዎችዎን ለማግኘት እንዲረዳቸው የዳሰሳ ጥናት እየሰሩ በማስመሰል ፎርም በማስሞላት መረጃዎችን በመመንተፍ ሊያጭበረብሩ ይችላሉ።


የጥንቃቄ መልዕክቶቹ መረጃ የተገኘው ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025