ደሴ፤መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፡-በደሴ ከተማ ህብረተሰቡን በማሳተፍ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት መስመር ላይ የአስፋልት ማንጠፍ ሥራ ተጀመረ።
የክልልና የደሴ ከተማ አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት የደሴ ከተማን ኮሪደርን ጨምሮ ሌሎችንም መሰረተ ልማቶች ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የደሴ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቃሲም አበራ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የኮሪደር ልማቱ በተያዘለት ጊዜ በጥራት እየተሰራ ነው፡፡
በተለይ ከሌሎች አጋር ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት መቻሉ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ጠቁመው፤በኮሪደር ልማቱ የቅድመ ዝግጅት ሥራው በአብዛኛው ተጠናቆ አስፋልት ማንጠፍ እንደተጀመረ ገልጸዋል፡፡
ለበርካታ ወገኖችም የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን ዋና ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።
የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሱለይማን እሸቱ በበኩላቸው፤ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ከተሞችን ይበልጥ ውብና ለነዋሪዎች ምቹ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል።
የደሴ ከተማ የኮሪደር ልማትም በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑን ዛሬ በመስክ ምልከታ አረጋግጠናል ብለዋል፡፡
በተለይ ህብረተሰቡን በማሳተፍና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማቱ ለሌሎች ከተሞችም ምሳሌ በመሆን ልምድ የሚወሰድበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በልማቱ የብስክሌትና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ ሌሎቸንም አረንጓዴ ሥፍራዎችና መዝነኛዎች እየተሰሩ በመሆኑ ተደስተናል ያሉት አቶ ሱለይማን፤ ክልሉም ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እያደረገ ነው ብለዋል፡፡
በደሴ የኮሪደር ልማቱ ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት- ወሎ ባህል አምባ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚጠጋ መንገድ እንደሚሸፍን ታውቋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025