
ደሴ፤መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፡-በደሴ ከተማ ህብረተሰቡን በማሳተፍ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት መስመር ላይ የአስፋልት ማንጠፍ ሥራ ተጀመረ።
የክልልና የደሴ ከተማ አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት የደሴ ከተማን ኮሪደርን ጨምሮ ሌሎችንም መሰረተ ልማቶች ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የደሴ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቃሲም አበራ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የኮሪደር ልማቱ በተያዘለት ጊዜ በጥራት እየተሰራ ነው፡፡
በተለይ ከሌሎች አጋር ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት መቻሉ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ጠቁመው፤በኮሪደር ልማቱ የቅድመ ዝግጅት ሥራው በአብዛኛው ተጠናቆ አስፋልት ማንጠፍ እንደተጀመረ ገልጸዋል፡፡
ለበርካታ ወገኖችም የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን ዋና ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።
የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሱለይማን እሸቱ በበኩላቸው፤ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ከተሞችን ይበልጥ ውብና ለነዋሪዎች ምቹ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል።
የደሴ ከተማ የኮሪደር ልማትም በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑን ዛሬ በመስክ ምልከታ አረጋግጠናል ብለዋል፡፡
በተለይ ህብረተሰቡን በማሳተፍና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማቱ ለሌሎች ከተሞችም ምሳሌ በመሆን ልምድ የሚወሰድበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በልማቱ የብስክሌትና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ ሌሎቸንም አረንጓዴ ሥፍራዎችና መዝነኛዎች እየተሰሩ በመሆኑ ተደስተናል ያሉት አቶ ሱለይማን፤ ክልሉም ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እያደረገ ነው ብለዋል፡፡
በደሴ የኮሪደር ልማቱ ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት- ወሎ ባህል አምባ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚጠጋ መንገድ እንደሚሸፍን ታውቋል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025