
ደሴ፤መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፡-በደሴ ከተማ ህብረተሰቡን በማሳተፍ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት መስመር ላይ የአስፋልት ማንጠፍ ሥራ ተጀመረ።
የክልልና የደሴ ከተማ አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት የደሴ ከተማን ኮሪደርን ጨምሮ ሌሎችንም መሰረተ ልማቶች ዛሬ ጎብኝተዋል፡፡
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የደሴ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቃሲም አበራ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ ህብረተሰቡን በማሳተፍ የኮሪደር ልማቱ በተያዘለት ጊዜ በጥራት እየተሰራ ነው፡፡
በተለይ ከሌሎች አጋር ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት መቻሉ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ጠቁመው፤በኮሪደር ልማቱ የቅድመ ዝግጅት ሥራው በአብዛኛው ተጠናቆ አስፋልት ማንጠፍ እንደተጀመረ ገልጸዋል፡፡
ለበርካታ ወገኖችም የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን ዋና ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።
የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሱለይማን እሸቱ በበኩላቸው፤ በክልሉ የተለያዩ ከተሞች እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ከተሞችን ይበልጥ ውብና ለነዋሪዎች ምቹ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል።
የደሴ ከተማ የኮሪደር ልማትም በፍጥነትና በጥራት እየተከናወነ መሆኑን ዛሬ በመስክ ምልከታ አረጋግጠናል ብለዋል፡፡
በተለይ ህብረተሰቡን በማሳተፍና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማቱ ለሌሎች ከተሞችም ምሳሌ በመሆን ልምድ የሚወሰድበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በልማቱ የብስክሌትና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ ሌሎቸንም አረንጓዴ ሥፍራዎችና መዝነኛዎች እየተሰሩ በመሆኑ ተደስተናል ያሉት አቶ ሱለይማን፤ ክልሉም ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እያደረገ ነው ብለዋል፡፡
በደሴ የኮሪደር ልማቱ ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት- ወሎ ባህል አምባ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚጠጋ መንገድ እንደሚሸፍን ታውቋል፡፡
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026