ሰቆጣ፤መጋቢት 8/2017 (ኢዜአ)፦በዋግ ኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በጀነሬተር የሚሰሩ የውሃ ተቋማት በፀሐይ ሀይል እንዲሰሩ በመደረጉ የውሃ አቅርቦቱ መሻሻሉን የአስተዳደሩ ውሃና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ሃላፊ ዲያቆን አብርሃም አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት በብሔረሰብ አስተዳደሩ የተገነቡት አብዛኞቹ የውሃ ተቋማት በጀኔሬተርና በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰሩ ናቸው።
እነዚህ ተቋማት የነዳጅ ዋጋ ጭማሬ ሲደረግና የኤሌክትሪክ ሀይል ሲቋረጥ የሚቆሙበት ሁኔታ እንዳለ ገልጸው፣ በዚህም ህብረተሰቡ የወንዝ ውሃን ለመቅዳት ጊዜና ጉልበቱን ያባክን እንደነበር አውስተዋል።
ባለፉት ሰባት ወራትም ችግሩን በመሰረታዊነት ለመፍታ ስምንት የውሃ ተቋማትን ወደ ጸሐይ ሀይል በመቀየር የውሃ አቅርቦት እንዲጠናከር መሰራቱን ገልጸዋል።
በዚህም ከ80 ሚሊዮን 256 ሺህ ብር በላይ ወጭ በማድረግ የሀይል አቅርቦቱን ወደ ጸሐይ ሀይል መቀየሩን ገልጸዋል።
በዚህም 86ሺህ 484 የህብረተሰብ ክፍሎችን ያልተቋረጠ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ መቻሉን መምሪያ ሃላፊው አስረድተዋል።
በአሁኑ ወቅትም በጋዝጊብላና ሰሃላ ወረዳዎች ያሉ የውሃ ተቋማትኝ በጸሐይ ሀይል እንዲሰሩ የማድረግ ሥራው እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።
በአበርገሌ ወረዳ የኒሯቅ ከተማ የሚኖሩት አቶ ገብሬ ሚሰነ እንደገለጹት በአካባቢያቸው ያለው የውሃ ተቋም በጸሐይ ሀይል እንዲሰራ ከተደረገ ወዲህ የመጠጥ ውሃ ሳይቋረጥ እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአካባቢያቸው የተሰራው የጸሐይ ሀይል ማመንጫም በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጥም አስፈላጊውን ጥበቃ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ሌላዋ የእዚሁ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ሰርካለም ሃላዩ በበኩላቸው፣ የአካባቢያቸው የውሃ ተቋም በጸሐይ ሀይል መስራት ከጀመረ ወዲህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦቱ መሻሻሉን ነው የገለጹት።
"ከዚህ ቀደም በኤሌክትሪክ ሀይል ይሰራ የነበረው የውሃ ተቋሙ ሀይል ሲቋረጥ አገልግሎቱም አብሮ ስለሚቋረጥ የወንዝ ውሃ ለመጠቀም እንገደድ ነበር" ብለዋል።
በእዚህም ለውሃ ወለድና ሌሎች በሽታዎች ይጋለጡ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት ችግራቸው መፈታቱን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025