
ሰቆጣ፤መጋቢት 8/2017 (ኢዜአ)፦በዋግ ኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በጀነሬተር የሚሰሩ የውሃ ተቋማት በፀሐይ ሀይል እንዲሰሩ በመደረጉ የውሃ አቅርቦቱ መሻሻሉን የአስተዳደሩ ውሃና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ሃላፊ ዲያቆን አብርሃም አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት በብሔረሰብ አስተዳደሩ የተገነቡት አብዛኞቹ የውሃ ተቋማት በጀኔሬተርና በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰሩ ናቸው።
እነዚህ ተቋማት የነዳጅ ዋጋ ጭማሬ ሲደረግና የኤሌክትሪክ ሀይል ሲቋረጥ የሚቆሙበት ሁኔታ እንዳለ ገልጸው፣ በዚህም ህብረተሰቡ የወንዝ ውሃን ለመቅዳት ጊዜና ጉልበቱን ያባክን እንደነበር አውስተዋል።
ባለፉት ሰባት ወራትም ችግሩን በመሰረታዊነት ለመፍታ ስምንት የውሃ ተቋማትን ወደ ጸሐይ ሀይል በመቀየር የውሃ አቅርቦት እንዲጠናከር መሰራቱን ገልጸዋል።
በዚህም ከ80 ሚሊዮን 256 ሺህ ብር በላይ ወጭ በማድረግ የሀይል አቅርቦቱን ወደ ጸሐይ ሀይል መቀየሩን ገልጸዋል።
በዚህም 86ሺህ 484 የህብረተሰብ ክፍሎችን ያልተቋረጠ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ መቻሉን መምሪያ ሃላፊው አስረድተዋል።
በአሁኑ ወቅትም በጋዝጊብላና ሰሃላ ወረዳዎች ያሉ የውሃ ተቋማትኝ በጸሐይ ሀይል እንዲሰሩ የማድረግ ሥራው እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።
በአበርገሌ ወረዳ የኒሯቅ ከተማ የሚኖሩት አቶ ገብሬ ሚሰነ እንደገለጹት በአካባቢያቸው ያለው የውሃ ተቋም በጸሐይ ሀይል እንዲሰራ ከተደረገ ወዲህ የመጠጥ ውሃ ሳይቋረጥ እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአካባቢያቸው የተሰራው የጸሐይ ሀይል ማመንጫም በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጥም አስፈላጊውን ጥበቃ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ሌላዋ የእዚሁ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ሰርካለም ሃላዩ በበኩላቸው፣ የአካባቢያቸው የውሃ ተቋም በጸሐይ ሀይል መስራት ከጀመረ ወዲህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦቱ መሻሻሉን ነው የገለጹት።
"ከዚህ ቀደም በኤሌክትሪክ ሀይል ይሰራ የነበረው የውሃ ተቋሙ ሀይል ሲቋረጥ አገልግሎቱም አብሮ ስለሚቋረጥ የወንዝ ውሃ ለመጠቀም እንገደድ ነበር" ብለዋል።
በእዚህም ለውሃ ወለድና ሌሎች በሽታዎች ይጋለጡ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት ችግራቸው መፈታቱን ተናግረዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025