የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአስተዳደሩ በጀነሬተር ሲሰሩ የነበሩ የውሃ ተቋማት በሐሀይ ሀይል እንዲሰሩ በመደረጉ የውሃ አቅርቦቱ ተሻሽሏል

Mar 18, 2025

IDOPRESS

ሰቆጣ፤መጋቢት 8/2017 (ኢዜአ)፦በዋግ ኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በጀነሬተር የሚሰሩ የውሃ ተቋማት በፀሐይ ሀይል እንዲሰሩ በመደረጉ የውሃ አቅርቦቱ መሻሻሉን የአስተዳደሩ ውሃና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ።


የመምሪያው ሃላፊ ዲያቆን አብርሃም አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት በብሔረሰብ አስተዳደሩ የተገነቡት አብዛኞቹ የውሃ ተቋማት በጀኔሬተርና በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰሩ ናቸው።


እነዚህ ተቋማት የነዳጅ ዋጋ ጭማሬ ሲደረግና የኤሌክትሪክ ሀይል ሲቋረጥ የሚቆሙበት ሁኔታ እንዳለ ገልጸው፣ በዚህም ህብረተሰቡ የወንዝ ውሃን ለመቅዳት ጊዜና ጉልበቱን ያባክን እንደነበር አውስተዋል።


ባለፉት ሰባት ወራትም ችግሩን በመሰረታዊነት ለመፍታ ስምንት የውሃ ተቋማትን ወደ ጸሐይ ሀይል በመቀየር የውሃ አቅርቦት እንዲጠናከር መሰራቱን ገልጸዋል።


በዚህም ከ80 ሚሊዮን 256 ሺህ ብር በላይ ወጭ በማድረግ የሀይል አቅርቦቱን ወደ ጸሐይ ሀይል መቀየሩን ገልጸዋል።


በዚህም 86ሺህ 484 የህብረተሰብ ክፍሎችን ያልተቋረጠ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ መቻሉን መምሪያ ሃላፊው አስረድተዋል።


በአሁኑ ወቅትም በጋዝጊብላና ሰሃላ ወረዳዎች ያሉ የውሃ ተቋማትኝ በጸሐይ ሀይል እንዲሰሩ የማድረግ ሥራው እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።


በአበርገሌ ወረዳ የኒሯቅ ከተማ የሚኖሩት አቶ ገብሬ ሚሰነ እንደገለጹት በአካባቢያቸው ያለው የውሃ ተቋም በጸሐይ ሀይል እንዲሰራ ከተደረገ ወዲህ የመጠጥ ውሃ ሳይቋረጥ እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በአካባቢያቸው የተሰራው የጸሐይ ሀይል ማመንጫም በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጥም አስፈላጊውን ጥበቃ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ሌላዋ የእዚሁ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ሰርካለም ሃላዩ በበኩላቸው፣ የአካባቢያቸው የውሃ ተቋም በጸሐይ ሀይል መስራት ከጀመረ ወዲህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦቱ መሻሻሉን ነው የገለጹት።


"ከዚህ ቀደም በኤሌክትሪክ ሀይል ይሰራ የነበረው የውሃ ተቋሙ ሀይል ሲቋረጥ አገልግሎቱም አብሮ ስለሚቋረጥ የወንዝ ውሃ ለመጠቀም እንገደድ ነበር" ብለዋል።


በእዚህም ለውሃ ወለድና ሌሎች በሽታዎች ይጋለጡ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት ችግራቸው መፈታቱን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026