
ሰቆጣ፤መጋቢት 8/2017 (ኢዜአ)፦በዋግ ኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በጀነሬተር የሚሰሩ የውሃ ተቋማት በፀሐይ ሀይል እንዲሰሩ በመደረጉ የውሃ አቅርቦቱ መሻሻሉን የአስተዳደሩ ውሃና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ሃላፊ ዲያቆን አብርሃም አሰፋ ለኢዜአ እንደገለጹት በብሔረሰብ አስተዳደሩ የተገነቡት አብዛኞቹ የውሃ ተቋማት በጀኔሬተርና በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰሩ ናቸው።
እነዚህ ተቋማት የነዳጅ ዋጋ ጭማሬ ሲደረግና የኤሌክትሪክ ሀይል ሲቋረጥ የሚቆሙበት ሁኔታ እንዳለ ገልጸው፣ በዚህም ህብረተሰቡ የወንዝ ውሃን ለመቅዳት ጊዜና ጉልበቱን ያባክን እንደነበር አውስተዋል።
ባለፉት ሰባት ወራትም ችግሩን በመሰረታዊነት ለመፍታ ስምንት የውሃ ተቋማትን ወደ ጸሐይ ሀይል በመቀየር የውሃ አቅርቦት እንዲጠናከር መሰራቱን ገልጸዋል።
በዚህም ከ80 ሚሊዮን 256 ሺህ ብር በላይ ወጭ በማድረግ የሀይል አቅርቦቱን ወደ ጸሐይ ሀይል መቀየሩን ገልጸዋል።
በዚህም 86ሺህ 484 የህብረተሰብ ክፍሎችን ያልተቋረጠ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ መቻሉን መምሪያ ሃላፊው አስረድተዋል።
በአሁኑ ወቅትም በጋዝጊብላና ሰሃላ ወረዳዎች ያሉ የውሃ ተቋማትኝ በጸሐይ ሀይል እንዲሰሩ የማድረግ ሥራው እየተከናወነ መሆኑንም ገልጸዋል።
በአበርገሌ ወረዳ የኒሯቅ ከተማ የሚኖሩት አቶ ገብሬ ሚሰነ እንደገለጹት በአካባቢያቸው ያለው የውሃ ተቋም በጸሐይ ሀይል እንዲሰራ ከተደረገ ወዲህ የመጠጥ ውሃ ሳይቋረጥ እያገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአካባቢያቸው የተሰራው የጸሐይ ሀይል ማመንጫም በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጥም አስፈላጊውን ጥበቃ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ሌላዋ የእዚሁ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ሰርካለም ሃላዩ በበኩላቸው፣ የአካባቢያቸው የውሃ ተቋም በጸሐይ ሀይል መስራት ከጀመረ ወዲህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦቱ መሻሻሉን ነው የገለጹት።
"ከዚህ ቀደም በኤሌክትሪክ ሀይል ይሰራ የነበረው የውሃ ተቋሙ ሀይል ሲቋረጥ አገልግሎቱም አብሮ ስለሚቋረጥ የወንዝ ውሃ ለመጠቀም እንገደድ ነበር" ብለዋል።
በእዚህም ለውሃ ወለድና ሌሎች በሽታዎች ይጋለጡ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት ችግራቸው መፈታቱን ተናግረዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026