ተፈጥሮ እና የሰው ጥበብ ተዋሕደው የባሕር ዳርን ውበት ይበልጥ እያወጡት ነው።
ከተማዋን የንግድና የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ አመራሩ እየጣረ ነው።
ባሕር ዳር በፈተና ውስጥ የመጽናት ምሳሌ ናት፤ ባለፉት ዓመታት የነበረው ፈተና እያለፈ ነው። ባሕር ዳር በፈተናው ውስጥ ሥራዋን አላቋረጠችም።
ለፈተና የተወረወረውን ድንጋይ ለግንባታ ተጠቅማበታለች።
የጣና መከፈት የማስተሣሠር(ኮኔክቲቪቲ) መርሐችን መገለጫ ነው።
የልማት ሥራዎቻችን መመጋገብ እና መተሣሠር እንዳለባቸው የባሕር ዳር ኮሪደር ምሳሌ ይሆናል።
ለብዙ ዘመናት ከከተማው ተለያይቶ የነበረው ጣና ወደ ስምንት በሚደርሱ ቦታዎች ከኮሪደሩ ጋር ተገናኝቷል። ይህም ከመዝናኛነቱ ባሻገር ከተማዋን ነፋሻማ አድርጓታል።
በመደመር መንገድ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በነባር ዕሴቶቻችን ላይ አዳዲስ ዕሴቶችን ጨምረን መገንባት አለብን።
ባሕርዳር የጣና ሐይቅና የዓባይ ወንዝ መገናኛ ናት።
ከግማሽ ምእተ ዓመት በላይ ያስቆጠሩ የዘንባባ ዛፎች አሏት። በዚህ ላይ የኮሪደር ልማቱ ለባሕር ዳር ተጨማሪ ውበት ሰጥቷታል።
የአካባቢ ተቋማት ፈጠራ እየጨመሩ ልማትን እንዲያሣልጡ ማድረግ፤
በባሕር ዳር ኮሪደር የለበሱት ንጣፎች እና የቆሙት መብራቶች በአካባቢው ተቋማትና ባለሞያዎች የተዘጋጁ ናቸው።
በቀጣይም አካባቢያዊ ክሂሎትንና ዐቅምን መጠቀም የበለጠ መለመድ አለበት።
ባሕርዳርን የስፖርትና የቅርስ ቱሪዝም መዳረሻ ማድረግ፦ በጣና ዙሪያ ያሉት ታሪካዊ ሥፍራዎች፤ ከጣናና ከዓባይ ጋር ተያይዘው የተሠሩት ወደቦችና መናፈሻዎች፤ የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም፣ የዓባይ ዘመናዊ ድልድይ እና ሌሎቹም ልማቶች ባሕር ዳርን የ22ኛው መክዘ የንግድና ቱሪዝም ማዕከል እያደረጓት ነው።
የአመራር አርአያነት፦ አመራር ሠርቶ የሚያሠራ፣ ቀድሞ የሚያስከትል መሆን አለበት።
የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት የራሳቸውን ጽህፈት ቤት አካባቢ አስተካክለው ኮሪደሩን በመሥራት አርአያ መሆናቸው ትምህርት የሚሆን ነው።
ባሕር ዳር ከዚህም በላይ መሥራት የምትችል ናት። ይሄ መጀመሪያዋ እንጂ የመጨረሻዋ አይደለም።
ጽዳቱን ባህል ማድረግ፤ የተሠሩ አካባቢዎችን ጥንቅቅ ማድረግ፤ ተቋማት አካባቢያቸውን እንዲቀይሩ ማትጋት፤ ንግድን፣ ቱሪዝምንና ኢንቨስትመንትን ይበልጥ ማበረታታት፣ ከሕዝቡም ከአመራሩም ይጠበቃል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025