የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

መገናኛ ብዙሃን በዲጂታል ዓለም ቁልፍ ተዋናይ ሊሆኑ ይገባል- ሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

Mar 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ)፦ ዓለም ዲጂታል መልክ በያዘበት በዚህ ዘመን መገናኛ ብዙሃን የዘርፉ ቁልፍ ተዋናይ ሊሆኑ እንደሚገባ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ገለጹ።

የአማርኛ ፌስቡክ ገጽ ተከታይ 4 ሚሊየን መሻገሩን ተከትሎ “ፋና ሚዲያ ዲጂታል ዐርበኛ” በሚል መሪ ሐሳብ የማበረታቻና ዕውቅና መርሐ ግብር ተካሂዷል።

አማካሪ ሚኒስትሩና የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ ሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ የተቋሙ አመራሮች፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የዲጂታል ሚዲያ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።


አማካሪ ሚኒስትሩና የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ ሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በወቅቱ እንዳሉት ዓለም ወደ ዲጂታል በመለወጡ ሚዲያው በድሮ አሰራር ብቻ መቀጠል አይቻልም።

የአዲሱ ትውልዱ ቋንቋ ወደ ዲጂታል ዓለም እየተለወጠ መምጣቱን ጠቅሰው፤ መገናኛ ብዙሃን ዲጂታል ዘርፍ በሁሉም ፕላትፎርሞች ተጠናክሮ መውጣት እንዳለበት አንስተዋል።

ሚዲያ የነገ መልክ የሚቀርጽ በመሆኑ የዲጂታል ዓለም ውስጥ ዋኝቶ ለመሻገር በዘርፉ ቁልፍ ተዋናይ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።

እንደ ሀገር የሚዲያዎችን የዲጂታል አቅም ለማጎልበት በሰው ኃይል የማብቃት፣ ተደራሽነትና የቴክኖሎጂ አቅምን የማሳደግ ስራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ ተደራሽነትን ለማሳደግ በርካታ ስራዎች በመሰራቱ ዕውቅናው እንደተሰጠ ጠቅሰዋል።

ኢዜአን ጨምሮ ባለፉት ወራት የዲጂታል አቅም ለማጎልበት ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ሲሰራ መቆየቱን ገልጸው፤ ሁሉም ተቋማት በየፊናቸው በፈጣን ለውጥ ላይ መሆናቸውን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤ የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዲጂታል ቡድን የሰራው ስራ ውጤታማ መሆኑን አንስተው፤ ከ4 ሚሊየን የተሻገረ ተከታይ በማፍራታችሁ እንኳን ደስ አላችህ ብለዋል።

የሚዲያ ተቋማት ሕብረት ፈጥረው ፋና ላይ የመጣው ለውጥ ወደ ሌሎች ተቋማትም ሊስፋፋ እንደሚገባው አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጌትነት ታደሰ፤ የዲጂታል ሚዲያው ዘርፍ በሀገር ግንባታ ውስጥ የድርሻውን እንዲወጣ ሁሉም ሚናውን መጫወት እንዳለበት ጠቁመዋል።

ሁሉንም ሚዲያ አማራጮችና አቅም በማሰባሰብ ጥሩ ውጤት እየመጣ እንደሆነም ገልጸው፤ እንደ ሚዲያ ብንፎካከርም የምንሰራው ለአንድ ሀገር መሆኑ መረሳት የለበትም ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ መሳፍንት ተፈራ በበኩላቸው÷ ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ እያስመዘገበ ያለውን ውጤት አድንቀው፣ በቀጣይም የበለጠ መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።

ዘመናዊ የሆነው የዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ በባህላዊ መንገድ ጥቅም ላይ ሲውል እንደነበር አንስተው÷ ዘመኑን መስሎ መጓዝ እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026