
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ):- የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በኢትዮጵያ መጀመሪያ የሆነውን የታካሚዎች የሜዲካል ቦርድ የዲጂታል ሰርተፊኬት አገልግሎትን ዛሬ በይፋ አስጀምሯል።
ሰርተፍኬቱ በወረቀት ሲሰጥ የነበረውን የታካሚዎች ሜዲካል ቦርድ አሰራር የሚያስቀር ነው።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ እና የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ የአገልግሎቱ መጀመር ወደ ውጭ ሀገር ሄደው ህክምና ለሚፈልጉ ታካሚዎች እንግልት የሚቀንስና የአገልግሎት ፈላጊዎችን እርካታ የሚጨምር መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም የሆስፒታሉን የአገልግሎት አሰጣጥ ይበልጥ የሚያሻሽል እንዲሁም የተሳሳቱ ማስረጃዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር አጋዥ እንደሆነ አመልክተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም የጤና ሚኒስቴር ወደ ውጭ ሀገር ሄደው ህክምና ለሚፈልጉ ታካሚዎች ወጥ በሆነ አሰራር ማስተናገድ የሚያስችል መመሪያ እያዘጋጀ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የሆስፒታሉ ሁሉንም አገልግሎቶች ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበው ለዚህም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሆስፒታሉ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚጠቀጥል ተናግረዋል።

የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አንዱዓለም ደነቀ ሆስፒታሉ የታካሚዎች የሜዲካል ቦርድ የዲጂታል ሰርተፊኬት አገልግሎት መስጠት መጀመሩ የተገልጋዮችን እርካታ እንደሚጨምር ገልጸዋል።
አገልግሎቱ የተጀመሩ የሜዲካል ሪከርድ ስርዓትን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚያግዝም አመልክተዋል።
የዲጂታል ሰርተፍኬቱ ስራ ሌሎች ሆስፒታሎች እና የጤና ተቋማት አገልግሎቱን እንዲጀምሩ በር ከፋች መሆኑንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም ማሪ ስቶፕስ ኢትዮጵያ ለጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከመወለጃ ቀናቸው አስቀድሞ ለሚወለዱ ጨቅላ ህፃናት ክብካቤ የሚያገለግሉ የህክምና ቁሳቁስ እንዲሁም ለማወለጃ ክፍል እድሳት የሚሆን ከሁለት ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል።
ዶክተር ደረጀ ድጋፉ የግል እና የመንግስት ተቋማት በትብብር መስራት እንደሚችሉ ማሳያ እንደሆነ መግለጻቸውን ከጤና ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026