
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሩሲያ ሞስኮ እየተካሄደ በሚገኘው 31ኛው የዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ኢንዱስትሪ አውደ ርዕይ ላይ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማስተዋወቅ ላይ ትገኛለች።
ከትናንት በስቲያ በተጀመረው አውደ ርዕይ ላይ ከ909 በላይ ኩባንያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
በሞስኮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በአውደ ርዕዩ ላይ የኢትዮጵያን ቱሪስት መዳረሻዎች እና የቡና ሀብት ለጎብኚዎች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛሉ።

ኤምባሲው ከሩሲያ ዋና ዋና አስጎብኚ ድርጅቶች ጋር ውይይት አካሂዷል።
ከ16 ሺህ በላይ ጎብኚዎች አውደ ርዕዩን እንደሚጎበኙት ይጠበቃል።
31ኛው የዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ኢንዱስትሪ አውደ ርዕይ ዛሬ እንደሚጠናቀቅ ኢዜአ በሞስኮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025