
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሩሲያ ሞስኮ እየተካሄደ በሚገኘው 31ኛው የዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ኢንዱስትሪ አውደ ርዕይ ላይ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማስተዋወቅ ላይ ትገኛለች።
ከትናንት በስቲያ በተጀመረው አውደ ርዕይ ላይ ከ909 በላይ ኩባንያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
በሞስኮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በአውደ ርዕዩ ላይ የኢትዮጵያን ቱሪስት መዳረሻዎች እና የቡና ሀብት ለጎብኚዎች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛሉ።

ኤምባሲው ከሩሲያ ዋና ዋና አስጎብኚ ድርጅቶች ጋር ውይይት አካሂዷል።
ከ16 ሺህ በላይ ጎብኚዎች አውደ ርዕዩን እንደሚጎበኙት ይጠበቃል።
31ኛው የዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ኢንዱስትሪ አውደ ርዕይ ዛሬ እንደሚጠናቀቅ ኢዜአ በሞስኮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026