የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት ወራት ከወጪ ንግድ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አገኝታለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Mar 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ባለፉት 8 ወራት ከሸቀጦች ወጪ ንግድ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ኢኮኖሚ ተኮር ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።

በማብራሪያቸውም ከወጪ ንግድ አንጻር ባለፉት ስምንት ወራት ኢትዮጵያ ያገኘችው ገቢ ከየትኛውም ዓመት የኤክስፖርት ገቢ እንደሚበልጥ ገልጸዋል።

በዚህም ኢትዮጵያ ለውጭ ገበያ ካቀረበቻቸው ምርቶች 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷን ነው የተናገሩት።

በሚቀጥሉት አራት ወራት ይህንን አስጠብቀን የምንሄድ ከሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ እመርታ ይመዘገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በ10 ዓመት ያስቀመጥነው ግብ እንደሚሳካም ማረጋገጫ ይሆናል ብለዋል።

ከሸቀጦች በተጨማሪ ከአገልግሎት ወጪ ንግድ 4 ነጥብ 7 ቢሊዮን፣ ከሬሚታንስ 3 ነጥብ 7 ቢሊዮን፣ ከውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት 2 ቢሊዮን ዶላር በስምንቱ ወራት መገኘቱንም ተናግረዋል።

በሌላ በኩል መንግሥት የሀገር ውስጥ ገቢና ታክስ መሰብሰብ አቅሙን እያሳደገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ባለፉት ስምንት ወራት ከ580 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸዋል።

መንግሥት መሰረተ ልማት የሚያስፋፋው ገቢ መሰብሰብ ከቻለ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሌሎች ሀገራት አንጻር የሚሰበሰበው ገቢ አሁንም ዝቅተኛ ነው ብለዋል።

ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ ከአበዳሪዎች ጋር በመደራደር 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የዕዳ ሽግሽግ እንደተደረገላትም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026