የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት ወራት ከወጪ ንግድ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አገኝታለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Mar 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ባለፉት 8 ወራት ከሸቀጦች ወጪ ንግድ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ኢኮኖሚ ተኮር ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።

በማብራሪያቸውም ከወጪ ንግድ አንጻር ባለፉት ስምንት ወራት ኢትዮጵያ ያገኘችው ገቢ ከየትኛውም ዓመት የኤክስፖርት ገቢ እንደሚበልጥ ገልጸዋል።

በዚህም ኢትዮጵያ ለውጭ ገበያ ካቀረበቻቸው ምርቶች 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷን ነው የተናገሩት።

በሚቀጥሉት አራት ወራት ይህንን አስጠብቀን የምንሄድ ከሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ እመርታ ይመዘገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በ10 ዓመት ያስቀመጥነው ግብ እንደሚሳካም ማረጋገጫ ይሆናል ብለዋል።

ከሸቀጦች በተጨማሪ ከአገልግሎት ወጪ ንግድ 4 ነጥብ 7 ቢሊዮን፣ ከሬሚታንስ 3 ነጥብ 7 ቢሊዮን፣ ከውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት 2 ቢሊዮን ዶላር በስምንቱ ወራት መገኘቱንም ተናግረዋል።

በሌላ በኩል መንግሥት የሀገር ውስጥ ገቢና ታክስ መሰብሰብ አቅሙን እያሳደገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ባለፉት ስምንት ወራት ከ580 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸዋል።

መንግሥት መሰረተ ልማት የሚያስፋፋው ገቢ መሰብሰብ ከቻለ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሌሎች ሀገራት አንጻር የሚሰበሰበው ገቢ አሁንም ዝቅተኛ ነው ብለዋል።

ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ ከአበዳሪዎች ጋር በመደራደር 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የዕዳ ሽግሽግ እንደተደረገላትም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025