
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ባለፉት 8 ወራት ከሸቀጦች ወጪ ንግድ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ኢኮኖሚ ተኮር ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።
በማብራሪያቸውም ከወጪ ንግድ አንጻር ባለፉት ስምንት ወራት ኢትዮጵያ ያገኘችው ገቢ ከየትኛውም ዓመት የኤክስፖርት ገቢ እንደሚበልጥ ገልጸዋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ለውጭ ገበያ ካቀረበቻቸው ምርቶች 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷን ነው የተናገሩት።
በሚቀጥሉት አራት ወራት ይህንን አስጠብቀን የምንሄድ ከሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ እመርታ ይመዘገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በ10 ዓመት ያስቀመጥነው ግብ እንደሚሳካም ማረጋገጫ ይሆናል ብለዋል።
ከሸቀጦች በተጨማሪ ከአገልግሎት ወጪ ንግድ 4 ነጥብ 7 ቢሊዮን፣ ከሬሚታንስ 3 ነጥብ 7 ቢሊዮን፣ ከውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት 2 ቢሊዮን ዶላር በስምንቱ ወራት መገኘቱንም ተናግረዋል።
በሌላ በኩል መንግሥት የሀገር ውስጥ ገቢና ታክስ መሰብሰብ አቅሙን እያሳደገ መሆኑን ጠቅሰው፤ ባለፉት ስምንት ወራት ከ580 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸዋል።
መንግሥት መሰረተ ልማት የሚያስፋፋው ገቢ መሰብሰብ ከቻለ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሌሎች ሀገራት አንጻር የሚሰበሰበው ገቢ አሁንም ዝቅተኛ ነው ብለዋል።
ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ ከአበዳሪዎች ጋር በመደራደር 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የዕዳ ሽግሽግ እንደተደረገላትም ተናግረዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026