
ደብረ መርቆስ፤ መጋቢት 22/2017(ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን እስካሁን ከ13 ሺህ በላይ የተለያዩ የሃይል አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን የዞኑ ውሃና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ተወካይ ሃላፊ አቶ አምበሉ መሰሉ ለኢዜአ እንደገለጹት አርሶ አደሩ በታዳሽ ሃይል የሚሰሩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ኑሮውን እንዲያዘምን በትኩረት እየተሰራ ነው።
በበጀት ዓመቱ የታዳሽ ሃይል አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ተደራሽ ለማድረግ በተደረገው ጥረት እስካሁን ከ13ሺህ በላይ የሚሆነውን ማሳካት መቻሉንተናግረዋል።
ከቀረቡት የሃይል አማራጮች መካከልምየተሻሻሉ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎች፣ በጸሐይ ሃይል የሚሰሩ ቁሳቁሶችና የባዮ ጋዝ ግንባታ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል።
በዚህም ከስምንት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን አክለዋል።
የተለያዩ የሃይል አማራጮችን ተደራሽ በማድረግ የተከናወነው ተግባርካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ40 በመቶ በላይ ብልጫ እንዳለውም አስረድተዋል።
ውጤቱን ማስመዝገብ የተቻለው እየተሻሻለ የመጣውን የሰላም መስፈን በመጠቀም መንግስት፣ አጋር ድርጅቶችና አርሶ አደሮች በቅንጅት ባደረጉት ርብርብ መሆኑን አክለዋል።
ከአማራጭ የሃይል ምንጭ ተጠቃሚዎች መካከል በዞኑ የጎዛምን ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ትብለጥ አጥናፉ እንዳሉት በዚህ ዓመት የማገዶ ቆጣቢ ምድጃ መጠቀማቸውን ተናግረዋል።
በዚህም ለማገዶ ይወጣ የነበረው ወጪ ቀንሶላቸው ኑሯቸውን እንዳቀለለላቸው ገልጸዋል።
በዞኑ የደጀን ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ታምሩ ምረት በበኩላቸው በጸሃይ ሃይል የሚሰሩ የቤት መብራቶች እየተጠቀሙ እንደሆነ አስረድተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025