የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በዞኑ ከ13 ሺህ በላይ የተለያዩ የሃይል አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ማድረግ ተችሏል

Apr 3, 2025

IDOPRESS

ደብረ መርቆስ፤ መጋቢት 22/2017(ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን እስካሁን ከ13 ሺህ በላይ የተለያዩ የሃይል አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን የዞኑ ውሃና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ተወካይ ሃላፊ አቶ አምበሉ መሰሉ ለኢዜአ እንደገለጹት አርሶ አደሩ በታዳሽ ሃይል የሚሰሩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ኑሮውን እንዲያዘምን በትኩረት እየተሰራ ነው።

በበጀት ዓመቱ የታዳሽ ሃይል አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ተደራሽ ለማድረግ በተደረገው ጥረት እስካሁን ከ13ሺህ በላይ የሚሆነውን ማሳካት መቻሉንተናግረዋል።

ከቀረቡት የሃይል አማራጮች መካከልምየተሻሻሉ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎች፣ በጸሐይ ሃይል የሚሰሩ ቁሳቁሶችና የባዮ ጋዝ ግንባታ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል።

በዚህም ከስምንት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን አክለዋል።

የተለያዩ የሃይል አማራጮችን ተደራሽ በማድረግ የተከናወነው ተግባርካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ40 በመቶ በላይ ብልጫ እንዳለውም አስረድተዋል።

ውጤቱን ማስመዝገብ የተቻለው እየተሻሻለ የመጣውን የሰላም መስፈን በመጠቀም መንግስት፣ አጋር ድርጅቶችና አርሶ አደሮች በቅንጅት ባደረጉት ርብርብ መሆኑን አክለዋል።

ከአማራጭ የሃይል ምንጭ ተጠቃሚዎች መካከል በዞኑ የጎዛምን ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ትብለጥ አጥናፉ እንዳሉት በዚህ ዓመት የማገዶ ቆጣቢ ምድጃ መጠቀማቸውን ተናግረዋል።

በዚህም ለማገዶ ይወጣ የነበረው ወጪ ቀንሶላቸው ኑሯቸውን እንዳቀለለላቸው ገልጸዋል።

በዞኑ የደጀን ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ታምሩ ምረት በበኩላቸው በጸሃይ ሃይል የሚሰሩ የቤት መብራቶች እየተጠቀሙ እንደሆነ አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026