ደብረ መርቆስ፤ መጋቢት 22/2017(ኢዜአ)፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን እስካሁን ከ13 ሺህ በላይ የተለያዩ የሃይል አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን የዞኑ ውሃና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ተወካይ ሃላፊ አቶ አምበሉ መሰሉ ለኢዜአ እንደገለጹት አርሶ አደሩ በታዳሽ ሃይል የሚሰሩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ኑሮውን እንዲያዘምን በትኩረት እየተሰራ ነው።
በበጀት ዓመቱ የታዳሽ ሃይል አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ተደራሽ ለማድረግ በተደረገው ጥረት እስካሁን ከ13ሺህ በላይ የሚሆነውን ማሳካት መቻሉንተናግረዋል።
ከቀረቡት የሃይል አማራጮች መካከልምየተሻሻሉ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎች፣ በጸሐይ ሃይል የሚሰሩ ቁሳቁሶችና የባዮ ጋዝ ግንባታ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል።
በዚህም ከስምንት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን አክለዋል።
የተለያዩ የሃይል አማራጮችን ተደራሽ በማድረግ የተከናወነው ተግባርካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ40 በመቶ በላይ ብልጫ እንዳለውም አስረድተዋል።
ውጤቱን ማስመዝገብ የተቻለው እየተሻሻለ የመጣውን የሰላም መስፈን በመጠቀም መንግስት፣ አጋር ድርጅቶችና አርሶ አደሮች በቅንጅት ባደረጉት ርብርብ መሆኑን አክለዋል።
ከአማራጭ የሃይል ምንጭ ተጠቃሚዎች መካከል በዞኑ የጎዛምን ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ትብለጥ አጥናፉ እንዳሉት በዚህ ዓመት የማገዶ ቆጣቢ ምድጃ መጠቀማቸውን ተናግረዋል።
በዚህም ለማገዶ ይወጣ የነበረው ወጪ ቀንሶላቸው ኑሯቸውን እንዳቀለለላቸው ገልጸዋል።
በዞኑ የደጀን ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ታምሩ ምረት በበኩላቸው በጸሃይ ሃይል የሚሰሩ የቤት መብራቶች እየተጠቀሙ እንደሆነ አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025