
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት(ግሪን ሞቢሊቲ) እያከናወነችው ባለው ተግባር ለአፍሪካ ምሳሌ የሚሆን አቅም እየፈጠረች መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በረኦ ሀሰን ገለጹ።
መንግስት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ ለማምረት በአጭር እና ረጅም ጊዜ እቅዶች በርካታ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኝ ተመላክቷል፡፡
የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በረኦ ሀሰን ለኢዜአ እንደገለፁት፤ መንግስት አረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት በርካታ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡

ከዚህም ውስጥ የነዳጅ ትራንስፖርትን በኤሌክትሪክ ትራንስፖርት በመቀየር በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን የማስፋፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ መሙያ ቦታዎችን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በአጭር እና በረጅም ጊዜ እቅድ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም የሚያስችል ስትራቴጂ ተቀርጾ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት፡፡

ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪ ማምረት የሚያስችል የተፈጥሮ ሀብት ያላት በመሆኑ ሀብቱን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪ ለማምረት በረጅም ጊዜ እቅድ እየሰራች እንደምትገኝም ሚኒስትር ዴኤታው አመላክተዋል፡፡
ዓለም አቀፍ ተቋማት ሃብታቸውን እንዲያፈሱ ብሎም ልምዳቸውን እንዲያጋሩ መድረክ እየተፈጠረ ይገኛል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ኢትየጵያ ከ700 በላይ የአለም አቀፍ ተቋማትና ኤክስፖርተሮች እና አመራሮች የተገኙበት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ላይ ያተኮረ አለም አቀፍ ኮንፍረንስ ማካሄዷንም ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት(ግሪን ሞብሊቲ) ላይ እያከናወነች ባለችው ተግባር ለአፍሪካ ምሳሌ የሚሆን አቅም እየፈጠረች መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።
የህዝቡን ሰፊ የትራንስፖርት ጥያቄ ከመመለስ አንጻር ፍላጎትን መሰረት ያደረገ የኤሌክትሪክ መኪኖችን የመገጣጠም ስራ ትኩረት የተደረገበት መሆኑንም አንስተዋል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025