የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ለአፍሪካ ምሳሌ የሚሆን አቅም እየፈጠረች ነው - የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 26/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት(ግሪን ሞቢሊቲ) እያከናወነችው ባለው ተግባር ለአፍሪካ ምሳሌ የሚሆን አቅም እየፈጠረች መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በረኦ ሀሰን ገለጹ።

መንግስት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ ለማምረት በአጭር እና ረጅም ጊዜ እቅዶች በርካታ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኝ ተመላክቷል፡፡

የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በረኦ ሀሰን ለኢዜአ እንደገለፁት፤ መንግስት አረንጓዴ ትራንስፖርትን ለማስፋፋት በርካታ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡


ከዚህም ውስጥ የነዳጅ ትራንስፖርትን በኤሌክትሪክ ትራንስፖርት በመቀየር በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን የማስፋፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ መሙያ ቦታዎችን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

በአጭር እና በረጅም ጊዜ እቅድ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም የሚያስችል ስትራቴጂ ተቀርጾ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት፡፡


ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪ ማምረት የሚያስችል የተፈጥሮ ሀብት ያላት በመሆኑ ሀብቱን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪ ለማምረት በረጅም ጊዜ እቅድ እየሰራች እንደምትገኝም ሚኒስትር ዴኤታው አመላክተዋል፡፡

ዓለም አቀፍ ተቋማት ሃብታቸውን እንዲያፈሱ ብሎም ልምዳቸውን እንዲያጋሩ መድረክ እየተፈጠረ ይገኛል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ኢትየጵያ ከ700 በላይ የአለም አቀፍ ተቋማትና ኤክስፖርተሮች እና አመራሮች የተገኙበት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ላይ ያተኮረ አለም አቀፍ ኮንፍረንስ ማካሄዷንም ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት(ግሪን ሞብሊቲ) ላይ እያከናወነች ባለችው ተግባር ለአፍሪካ ምሳሌ የሚሆን አቅም እየፈጠረች መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።

የህዝቡን ሰፊ የትራንስፖርት ጥያቄ ከመመለስ አንጻር ፍላጎትን መሰረት ያደረገ የኤሌክትሪክ መኪኖችን የመገጣጠም ስራ ትኩረት የተደረገበት መሆኑንም አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026