
አዲስ አበባ ፤መጋቢት 26/2017(ኢዜአ)፦ መጋቢት 24 የትልሞቻችን ሁሉ የስኬት ጫፍ መጀመሪያ፣ የለውጥ ጮራ መባቻና የብልፅግና ዘመን ጅማሮ ነው ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ሰባት የለውጥ ዓመታትን በድል ተሻግረን የሰነቅናቸውን ታላላቅ ሕልሞች እያሳካን፣ የገጠሙንን ፈተናዎች ከህዝባችን ጋር በቅንጅት በመስራት እየተሻገርን፣ የመዳረሻ ተስፋዎቻችንን ወደ ሚጨበጥ ብርሃን እየቀየርን እና ለህዝባችን የሚበጁ አያሌ ተግባራትን እያከናወንን እንገኛለን ብለዋል።
መጋቢት 24 የትልሞቻችን ሁሉ የስኬት ጫፍ መጀመሪያ፣ የለውጥ ጮራ መባቻና የብልፅግና ዘመን ጅማሮ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በብልፅግና ዘመን ስብራቶቻችንን የሚጠግኑ፣ የምናባችንን ከፍታና የተስፋዎቻችን ጥልቀት የሚመጥኑ የለውጥ ስራዎች ጥልቀትና ጥራት ባለው መልኩ በከተማና በገጠር እየተከናወኑ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
መዳረሻዎቻችን ከመንገዶቻችን ጋር የተሰናሰሉ፣ የህዝባችንን ዘላቂ ተጠቃሚነት ማረጋገጣቸውን የሚመሰክሩ የለውጥ አሻራዎች ህያው ማሳያ ከተሞቻችን መካከል ደሴ አንዷ ናት በማለት በማሳያነት ጠቅሰዋል።

በደሴ ከተማ ከቧንቧ ውሃ አደባባይ እስከ ወሎ ባህል አምባ የሚደርስ 1 ነጥብ 89 ኪሎ ሜትር የሚሸፍንና 46 ነጥብ 5 ሜትር ስፋት ያለው የኮሪደር ልማት፣ ቅልጥፍናና ጥራትን የሚጨምር፣ አገልግሎትን የሚያሳልጥ እንዲሁም ደህንነትን የሚያስጠብቅ የስማርት ሲቲ ፕሮጀክትና ሌሎችም ተጠቃሽ የልማት ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026