የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

መጋቢት 24 የትልሞቻችን ሁሉ የስኬት ጫፍ መጀመሪያ፣ የለውጥ ጮራ መባቻና የብልፅግና ዘመን ጅማሮ ነው

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤መጋቢት 26/2017(ኢዜአ)፦ መጋቢት 24 የትልሞቻችን ሁሉ የስኬት ጫፍ መጀመሪያ፣ የለውጥ ጮራ መባቻና የብልፅግና ዘመን ጅማሮ ነው ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ሰባት የለውጥ ዓመታትን በድል ተሻግረን የሰነቅናቸውን ታላላቅ ሕልሞች እያሳካን፣ የገጠሙንን ፈተናዎች ከህዝባችን ጋር በቅንጅት በመስራት እየተሻገርን፣ የመዳረሻ ተስፋዎቻችንን ወደ ሚጨበጥ ብርሃን እየቀየርን እና ለህዝባችን የሚበጁ አያሌ ተግባራትን እያከናወንን እንገኛለን ብለዋል።

መጋቢት 24 የትልሞቻችን ሁሉ የስኬት ጫፍ መጀመሪያ፣ የለውጥ ጮራ መባቻና የብልፅግና ዘመን ጅማሮ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በብልፅግና ዘመን ስብራቶቻችንን የሚጠግኑ፣ የምናባችንን ከፍታና የተስፋዎቻችን ጥልቀት የሚመጥኑ የለውጥ ስራዎች ጥልቀትና ጥራት ባለው መልኩ በከተማና በገጠር እየተከናወኑ ነው ሲሉም ተናግረዋል።

መዳረሻዎቻችን ከመንገዶቻችን ጋር የተሰናሰሉ፣ የህዝባችንን ዘላቂ ተጠቃሚነት ማረጋገጣቸውን የሚመሰክሩ የለውጥ አሻራዎች ህያው ማሳያ ከተሞቻችን መካከል ደሴ አንዷ ናት በማለት በማሳያነት ጠቅሰዋል።


በደሴ ከተማ ከቧንቧ ውሃ አደባባይ እስከ ወሎ ባህል አምባ የሚደርስ 1 ነጥብ 89 ኪሎ ሜትር የሚሸፍንና 46 ነጥብ 5 ሜትር ስፋት ያለው የኮሪደር ልማት፣ ቅልጥፍናና ጥራትን የሚጨምር፣ አገልግሎትን የሚያሳልጥ እንዲሁም ደህንነትን የሚያስጠብቅ የስማርት ሲቲ ፕሮጀክትና ሌሎችም ተጠቃሽ የልማት ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025