አርባምንጭ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተኪ ምርቶችን በስፋትና በጥራት በማምረት የውጭ ምንዛሪን ለማዳን ከአምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
በክልሉ "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ጥላሁን ከበደ ተኪ ምርቶችን በስፋትና በጥራት በማምረት የውጭ ምንዛሪን ለማዳን ከአምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር በቅንጅት ይሠራል ብለዋል።
ለውጡ ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት ተግባራዊ የተደረገው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት እንዲመዘገብ የላቀ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸው ይህ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ዘርፉ የነበረበትን ማነቆ ለመፍታት እንደ መንግስት የተወሰዱ ቁርጠኛ እርምጃዎች እያስመዘገቡት ያለውን ውጤት የበለጠ ለማላቅ አምራች ኢንዱስትሪው የኢኮኖሚ ፖሊሲ ትኩረት አቅጣጫን ተከትሎ የመደገፍ ስራ ይሰራል ብለዋል።
ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የመስሪያ፣ የማምረቻ እና የመሸጫ ቦታዎችን በማመቻቸት እንዲሁም የፋይናንስና የገበያ ትስስር ችግሮች እንዲፈቱ ከዘርፉ አካላት ጋር በመነጋገርና በመወያየት መፍትሄ እያስቀመጥን እንሄዳለን ሲሉም ገልጸዋል።
የአምራች ኢንዱስትሪውን ሚና በማላቅ ሀገር በቀል ሀብቶችን ጥቅም ላይ በማዋል የውጭ ምንዛሪን በማዳን የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ ርብርብ እናደርጋለን ነው ያሉት።
የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ቦጋለ ቦሼ(ዶ/ር) አምራች ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግር የማዕዘን ድንጋይ መሆኑን ገልጸዋል።
ክልሉ ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት የአምራች ኢንዱስትሪውን የፋይናንስ፣ የገበያና የግብዓት አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት ተቋማዊ አደረጃጀትን በማጠናከርና የኢትዮጵያ ታምርት ስትሪንግ ኮሚቴ በማዋቀር ሰፊ ተግባር እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
አምራች ኢንዱስትሪውን በጥናትና በምርምር ለመደገፍ በክልሉ ከሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የመልማት አቅም ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱንና በዚህም የኢንዱስትሪ አቅም ልየታና አዋጭነት ጥናት ለማድረግ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
በመድረኩ የክልሉ ኢንዱስትሪ ቢሮ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ላይ በተከናወኑ ተግባራትና ተግዳሮቶች ዙሪያ ሰነድ የቀረበ ሲሆን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ የአምራች ኢንዱስትሪ ዕድሎችና ተግዳሮቶች ላይ ያተኮረ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025