የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ተኪ ምርቶችን በስፋትና በጥራት በማምረት የውጭ ምንዛሪን ለማዳን በቅንጅት እንሰራለን - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አርባምንጭ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ተኪ ምርቶችን በስፋትና በጥራት በማምረት የውጭ ምንዛሪን ለማዳን ከአምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።

በክልሉ "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ጥላሁን ከበደ ተኪ ምርቶችን በስፋትና በጥራት በማምረት የውጭ ምንዛሪን ለማዳን ከአምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር በቅንጅት ይሠራል ብለዋል።


ለውጡ ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት ተግባራዊ የተደረገው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት እንዲመዘገብ የላቀ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልጸው ይህ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ዘርፉ የነበረበትን ማነቆ ለመፍታት እንደ መንግስት የተወሰዱ ቁርጠኛ እርምጃዎች እያስመዘገቡት ያለውን ውጤት የበለጠ ለማላቅ አምራች ኢንዱስትሪው የኢኮኖሚ ፖሊሲ ትኩረት አቅጣጫን ተከትሎ የመደገፍ ስራ ይሰራል ብለዋል።

ለአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የመስሪያ፣ የማምረቻ እና የመሸጫ ቦታዎችን በማመቻቸት እንዲሁም የፋይናንስና የገበያ ትስስር ችግሮች እንዲፈቱ ከዘርፉ አካላት ጋር በመነጋገርና በመወያየት መፍትሄ እያስቀመጥን እንሄዳለን ሲሉም ገልጸዋል።

የአምራች ኢንዱስትሪውን ሚና በማላቅ ሀገር በቀል ሀብቶችን ጥቅም ላይ በማዋል የውጭ ምንዛሪን በማዳን የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ ርብርብ እናደርጋለን ነው ያሉት።


የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ቦጋለ ቦሼ(ዶ/ር) አምራች ኢንዱስትሪው ለኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግር የማዕዘን ድንጋይ መሆኑን ገልጸዋል።

ክልሉ ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት የአምራች ኢንዱስትሪውን የፋይናንስ፣ የገበያና የግብዓት አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት ተቋማዊ አደረጃጀትን በማጠናከርና የኢትዮጵያ ታምርት ስትሪንግ ኮሚቴ በማዋቀር ሰፊ ተግባር እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

አምራች ኢንዱስትሪውን በጥናትና በምርምር ለመደገፍ በክልሉ ከሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የመልማት አቅም ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱንና በዚህም የኢንዱስትሪ አቅም ልየታና አዋጭነት ጥናት ለማድረግ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

በመድረኩ የክልሉ ኢንዱስትሪ ቢሮ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ላይ በተከናወኑ ተግባራትና ተግዳሮቶች ዙሪያ ሰነድ የቀረበ ሲሆን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ የአምራች ኢንዱስትሪ ዕድሎችና ተግዳሮቶች ላይ ያተኮረ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025