የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ባለሥልጣኑ የኮንስትራክሽን ዘርፉን ለማዘመንና ለማሳደግ ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ለማዘመንና ለማሳደግ የሚከናወኑ ተግባራትን በመደገፍ ከዘርፉ ተዋናዮች ጋር በቅርበት እንደሚሠራ የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሙአዝ በድሩ(ዶ/ር) ገለጹ።

ባለስልጣኑ ከኤች.ኬ ቢዝነስ ግሩፕ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጋር በመተባበር የግንባታ ጥራትን ማስጠበቅ የሚያስችል ቴክኖሎጂ የማስተዋወቅ መርሃ ግብር አካሂዷል።


የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሙአዝ በድሩ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ባለስልጣኑ ለዘርፉ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እና ክትትል በማድረግ የግል እና የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ለኮንስትራክሽን ዘርፉ ዕድገት ሚናቸውን እንዲወጡ እየሰራ ነው።

ምርትን ለውጭ ገበያ የሚያቀርቡ ጠንካራና ተወዳዳሪ ኢንዱስትሪዎች መገንባት የሚቻለው ወደ ሀገር የሚገባ ምርትን የሚተኩ ኢንዱስትሪዎችን በመደገፍ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የኮንስትራክሽን ዘርፉ በኢኮኖሚ ዕድገትና ልማት ውስጥ ድርሻው የጎላ እንደሆነም ነው የጠቀሱት።


በዚህም ዘርፉ ወደ ዘመናዊነት እንዲሸጋገር አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅና የማቅረብ ተግባር እየተከናወነ ነው ብለዋል።

የግብዓት ፍላጎትን በሀገር ውስጥ ማሟላት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውንም ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።

ለአብነትም ዛሬ የተዋወቀው አዲስ የፕላስቲክ ጥሬ እቃ እና በወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶች መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል የሚሰራው ፎርምወርክ(የግንባታ ኮንክሪት ቅርጽ ማውጫ) ለዘርፉ መጎልበት ትልቅ እርምጃ ነው ብለዋል።

ምርቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተደግፎ የሚመረት በመሆኑ በዘርፉ ያለውን የኮንስትራክሽን ግብዓት ችግር ለመፍታት ከማገዙ ባለፈ ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የውጪ ምንዛሬን ማዳን ያስችላል ነው ያሉት።


የኤች.ኬ ቢዝነስ ግሩፕ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ብሩ ዊርቱ፥ የፕላስቲክ ፎርምወርክ የግንባታ ዘርፉን ተወዳዳሪነት እንደሚያሳድግ ገልጸዋል።


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ኢሳያስ ገብረዮሃንስ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የፕላስቲክ ፎርምዎርኩ ለህንፃ ግንባታ እና ሌሎች የመሰረተ ልማት ስራዎች የሚያስፈልግ ግብዓት ነው ብለዋል።

የኮንስትራክሽን ግብዓት የጥራት ችግርን የሚያቃልል እንደሆነም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025