
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለመፍጠር በጋራ እንደሚሰሩ አስታወቁ።
በጃይካ ከፍተኛ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አማካሪ አቱሺ ያማናካ የተመራ ልዑክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝቷል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ለልዑኩ አቀባበል በማድረግ ተቋሙ እየተገበራቸው ያሉ ሁሉን አቀፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዕቀፎች የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ጉብኝቱ ኢትዮጵያ እና ጃፓን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን ለሀገር ልማት ለመጠቀም ያላቸውን የትብብር ቁርጠኝነት በግልጽ የሚያመላክት ነው ብለዋል።
የጃይካ ልዑክ ለኢንስቲትዩቱ ስኬቶች አድናቆታቸውን መቸራቸውን ከኢኒስቲትዩቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ከጉብኝቱ ጎን ለጎን ሁለቱ ተቋማት የሀገር በቀል ቋንቋ አጠቃቀም፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ለግብርና እና ለኢንስቲትዩቱ የክህሎት ልማት ኢኒሼቲቮች መጠቀም ላይ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውም ተጠቁሟል።
የጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ(ጃይካ) ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ በኢትዮጵያ የልማት ፕሮጀክቶችና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ እየሰራ ይገኛል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025