
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለመፍጠር በጋራ እንደሚሰሩ አስታወቁ።
በጃይካ ከፍተኛ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አማካሪ አቱሺ ያማናካ የተመራ ልዑክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝቷል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ለልዑኩ አቀባበል በማድረግ ተቋሙ እየተገበራቸው ያሉ ሁሉን አቀፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዕቀፎች የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ጉብኝቱ ኢትዮጵያ እና ጃፓን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን ለሀገር ልማት ለመጠቀም ያላቸውን የትብብር ቁርጠኝነት በግልጽ የሚያመላክት ነው ብለዋል።
የጃይካ ልዑክ ለኢንስቲትዩቱ ስኬቶች አድናቆታቸውን መቸራቸውን ከኢኒስቲትዩቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ከጉብኝቱ ጎን ለጎን ሁለቱ ተቋማት የሀገር በቀል ቋንቋ አጠቃቀም፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ለግብርና እና ለኢንስቲትዩቱ የክህሎት ልማት ኢኒሼቲቮች መጠቀም ላይ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውም ተጠቁሟል።
የጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ(ጃይካ) ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ በኢትዮጵያ የልማት ፕሮጀክቶችና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ እየሰራ ይገኛል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026