የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ተቋማቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው ገለጹ

Apr 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለመፍጠር በጋራ እንደሚሰሩ አስታወቁ።

በጃይካ ከፍተኛ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አማካሪ አቱሺ ያማናካ የተመራ ልዑክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝቷል።


የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ለልዑኩ አቀባበል በማድረግ ተቋሙ እየተገበራቸው ያሉ ሁሉን አቀፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዕቀፎች የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ ጉብኝቱ ኢትዮጵያ እና ጃፓን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን ለሀገር ልማት ለመጠቀም ያላቸውን የትብብር ቁርጠኝነት በግልጽ የሚያመላክት ነው ብለዋል።

የጃይካ ልዑክ ለኢንስቲትዩቱ ስኬቶች አድናቆታቸውን መቸራቸውን ከኢኒስቲትዩቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ከጉብኝቱ ጎን ለጎን ሁለቱ ተቋማት የሀገር በቀል ቋንቋ አጠቃቀም፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ለግብርና እና ለኢንስቲትዩቱ የክህሎት ልማት ኢኒሼቲቮች መጠቀም ላይ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውም ተጠቁሟል።

የጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ(ጃይካ) ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ በኢትዮጵያ የልማት ፕሮጀክቶችና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ እየሰራ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026