የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ተቋማቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው ገለጹ

Apr 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለመፍጠር በጋራ እንደሚሰሩ አስታወቁ።

በጃይካ ከፍተኛ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አማካሪ አቱሺ ያማናካ የተመራ ልዑክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝቷል።


የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ለልዑኩ አቀባበል በማድረግ ተቋሙ እየተገበራቸው ያሉ ሁሉን አቀፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ማዕቀፎች የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ ጉብኝቱ ኢትዮጵያ እና ጃፓን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን ለሀገር ልማት ለመጠቀም ያላቸውን የትብብር ቁርጠኝነት በግልጽ የሚያመላክት ነው ብለዋል።

የጃይካ ልዑክ ለኢንስቲትዩቱ ስኬቶች አድናቆታቸውን መቸራቸውን ከኢኒስቲትዩቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ከጉብኝቱ ጎን ለጎን ሁለቱ ተቋማት የሀገር በቀል ቋንቋ አጠቃቀም፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ለግብርና እና ለኢንስቲትዩቱ የክህሎት ልማት ኢኒሼቲቮች መጠቀም ላይ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መወያየታቸውም ተጠቁሟል።

የጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ(ጃይካ) ከእ.አ.አ 1993 ጀምሮ በኢትዮጵያ የልማት ፕሮጀክቶችና ዓለም አቀፍ ትብብር ላይ እየሰራ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025