
መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮዽያ ህዝቦች ክልል በአሲዳማነት የተጠቃ 800 ሺህ ሄክታር መሬትን በማከም የአፈር ለምነትን ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ አማኑኤል አለሙ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ ከሚታረሰው መሬት ውስጥ 800ሺህ ሄክታር የሚሆነው በአሲዳማነት የተጠቃ ነው።
ይህም በምርትና ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ስላልው ችግሩን ለመፍታት ከክልሉ ግብርና ቢሮ ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በተለይ አሲዳማ አፈርን በኖራ፣ በቨርም ኮምፖስት፣ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ ማዳበሪያ የማከም ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ነው የገለጹት።
ከኢትዮዽያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ጋር በመቀናጀትም አሲዳማ አፈርን መቋቋም የሚችሉ የሰብል ዝርያዎችን ለማላመድም በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።
በአሲዳማነት ችግር ምርታማነታቸው የቀነሱ መሬቶችን በሻይ ቅጠልና በቡና ልማት ለመሸፈን ክልላዊ ኢኒሼቲቭ ተቀርጾ ወደ ትግበራ መገባቱንም አቶ አማኑኤል አውስተዋል።

በኢትዮዽያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የአፈርና ውሃ ምርምር ዳይሬክተር ተመስገን ደሳለኝ(ዶ/ር) በበኩላቸው እንደ ሀገር የአፈር አሲዳማነት ችግርን በዘላቂነት በመፍታት ምርታማነትን ለማሳደግ መሰራቱን ጠቁመዋል።
ለእዚህም ኢንስቲትዩቱ በየደረጃው ከሚገኙ የክልል ግብርና ምርምር ተቋማት፣ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በተለይም የሚሰጡት ምርት የቀነሱ መሬቶችን በቪርሚን ኮምፓስትና በኖራ በማከም የአፈሩን ለምነት ለመመለስ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
የአፈር አሲዳማነት ችግር ስጋት ሆኖ እንዳይቀጥል ዘላቂ የአፈር ለምነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ከሁሉም ባለድርሻ አካላት እንደሚጠበቅም ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026