
መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮዽያ ህዝቦች ክልል በአሲዳማነት የተጠቃ 800 ሺህ ሄክታር መሬትን በማከም የአፈር ለምነትን ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ አማኑኤል አለሙ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ ከሚታረሰው መሬት ውስጥ 800ሺህ ሄክታር የሚሆነው በአሲዳማነት የተጠቃ ነው።
ይህም በምርትና ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ስላልው ችግሩን ለመፍታት ከክልሉ ግብርና ቢሮ ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በተለይ አሲዳማ አፈርን በኖራ፣ በቨርም ኮምፖስት፣ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ ማዳበሪያ የማከም ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ነው የገለጹት።
ከኢትዮዽያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ጋር በመቀናጀትም አሲዳማ አፈርን መቋቋም የሚችሉ የሰብል ዝርያዎችን ለማላመድም በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።
በአሲዳማነት ችግር ምርታማነታቸው የቀነሱ መሬቶችን በሻይ ቅጠልና በቡና ልማት ለመሸፈን ክልላዊ ኢኒሼቲቭ ተቀርጾ ወደ ትግበራ መገባቱንም አቶ አማኑኤል አውስተዋል።

በኢትዮዽያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የአፈርና ውሃ ምርምር ዳይሬክተር ተመስገን ደሳለኝ(ዶ/ር) በበኩላቸው እንደ ሀገር የአፈር አሲዳማነት ችግርን በዘላቂነት በመፍታት ምርታማነትን ለማሳደግ መሰራቱን ጠቁመዋል።
ለእዚህም ኢንስቲትዩቱ በየደረጃው ከሚገኙ የክልል ግብርና ምርምር ተቋማት፣ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በተለይም የሚሰጡት ምርት የቀነሱ መሬቶችን በቪርሚን ኮምፓስትና በኖራ በማከም የአፈሩን ለምነት ለመመለስ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
የአፈር አሲዳማነት ችግር ስጋት ሆኖ እንዳይቀጥል ዘላቂ የአፈር ለምነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ከሁሉም ባለድርሻ አካላት እንደሚጠበቅም ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026