
ጭፍራ፣ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል የአፈርና ውሃ ጥበቃና እንክብካቤ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የፕላንና ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ዓሊ መሐመድ ገለጹ።
የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ የሚያስችል የምክክር መድረክ በአፋር ክልል ጭፍራ ወረዳ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

መድረኩን ያስጀመሩት አቶ ዓሊ እንዳሉት የዛሬው መድረክ በአገር ደረጃም ሆነ በክልሉ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ የሚደረጉትን ጥረቶችን የሚያግዝ ነው።
የተጀመረው የአፈር ጥበቃና እንክብካቤ ስራ በቀጣይነት ማጠናከር ክልሉ በምግብ ራሰን ለመቻል በሚያደርገው ርብርብ ውሰጥ አዎንታዊ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።
በክልሉ ደረጃ የተጀመሩትን የልማት ስራዎች ለማስቀጠልና ያሉትን መሬቶች ወደ እርሻ ስራዎች ለማስገባት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
በክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የተፈጥሮ ሃብት ዘርፍ ምክትል ሃላፊ አቶ ኡስማን መሐመድ በበኩላቸው እንደገለፁት በአሁኑ ወቅት ለአፈርና ውሃ ጥበቃ እና እንክብካቤ ሥራ ትኩረት በማድረግ የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነትን ለመቀነስ እየተሰራ ነው።

ይህም መሬትን ለእርሻ ስራ እንዲያመች በማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው በዚህ ዓመት በክልል ደረጃ በ10 ወረዳዎች ላይ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ከእነዚህ ውሰጥ ሞዴል በሆነው ጭፍራ ወረዳ ገሪሮ ቀበሌ ላይ ከ2 ሺህ 400 ሄክታር በላይ የማገገሚያ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።
በዚህም ከሁለት ሺህ በላይ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማሳተፍ የተራቆተውን መሬት ወደ ነበረበት ለመመለስ የሚያስችል የንቅናቄ መርሃ ግብር ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በተገኙበት መጀመሩን አስታውሰዋል።
ይህ ክንውን በምግብ ራስን ለመቻል ለሚደረገው ጥረት አጋዥነት ያለው መሆኑንም አመላክተዋል።
ወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ባዘጋጀው በዚሁ መድረክ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ከግብርና ሚኒስቴርና ከአካባቢ ጥበቃ ባለ ስልጣን ፤ ከግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የመጡ ተወካዮችና የአካባቢው ማህበረሰብ ተገኝተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025