
ጭፍራ፣ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል የአፈርና ውሃ ጥበቃና እንክብካቤ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የፕላንና ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ዓሊ መሐመድ ገለጹ።
የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ የሚያስችል የምክክር መድረክ በአፋር ክልል ጭፍራ ወረዳ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

መድረኩን ያስጀመሩት አቶ ዓሊ እንዳሉት የዛሬው መድረክ በአገር ደረጃም ሆነ በክልሉ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቀነስ የሚደረጉትን ጥረቶችን የሚያግዝ ነው።
የተጀመረው የአፈር ጥበቃና እንክብካቤ ስራ በቀጣይነት ማጠናከር ክልሉ በምግብ ራሰን ለመቻል በሚያደርገው ርብርብ ውሰጥ አዎንታዊ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።
በክልሉ ደረጃ የተጀመሩትን የልማት ስራዎች ለማስቀጠልና ያሉትን መሬቶች ወደ እርሻ ስራዎች ለማስገባት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
በክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የተፈጥሮ ሃብት ዘርፍ ምክትል ሃላፊ አቶ ኡስማን መሐመድ በበኩላቸው እንደገለፁት በአሁኑ ወቅት ለአፈርና ውሃ ጥበቃ እና እንክብካቤ ሥራ ትኩረት በማድረግ የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነትን ለመቀነስ እየተሰራ ነው።

ይህም መሬትን ለእርሻ ስራ እንዲያመች በማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው በዚህ ዓመት በክልል ደረጃ በ10 ወረዳዎች ላይ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ከእነዚህ ውሰጥ ሞዴል በሆነው ጭፍራ ወረዳ ገሪሮ ቀበሌ ላይ ከ2 ሺህ 400 ሄክታር በላይ የማገገሚያ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።
በዚህም ከሁለት ሺህ በላይ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማሳተፍ የተራቆተውን መሬት ወደ ነበረበት ለመመለስ የሚያስችል የንቅናቄ መርሃ ግብር ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በተገኙበት መጀመሩን አስታውሰዋል።
ይህ ክንውን በምግብ ራስን ለመቻል ለሚደረገው ጥረት አጋዥነት ያለው መሆኑንም አመላክተዋል።
ወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ባዘጋጀው በዚሁ መድረክ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ከግብርና ሚኒስቴርና ከአካባቢ ጥበቃ ባለ ስልጣን ፤ ከግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የመጡ ተወካዮችና የአካባቢው ማህበረሰብ ተገኝተዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026