አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ለወሎ ተርሸሪ ኬር የህክምና እና የማስተማሪያ ሆስፒታል ግንባታ የተሰበሰበ ገንዘብና ንብረት የፋይናንስ ኦዲት በማከናወን እስከ ግንቦት 15 ድረስ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ርክክብ እንዲፈፀም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
የወሎ ተርሸሪ ኬርና የማስተማሪያ ሆስፒታል ፕሮጀክት በጎ አድራጎት ኮሚቴ ከወሎ ዩኒቨርሲቲ ጋር ፕሮጀክት ጽህፈት ቤቱን ለመዝጋት የሚደረግ የገንዘብና የንብረት የቅድመ ርክክብ ውይይት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
በመድረኩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር)፣ የኢፌዴሪ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን ቢራቱ፣ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አወል ስዒድ (ዶ/ር) የወሎ ተርሸሪ ኬር እና የማስተማሪያ የወሎ ሆስፒታል በጎ አድራጎት ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ጣይቱ ዓሊ እና የአከባቢው ማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።
በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ዩኒቨርሲቲው የወሎ ተርሸሪ ኬር የህክምና እና የማስተማሪያ ሆስፒታል ስም የተሰበሰበ ገንዘብ እንዲረከብ ከወራት በፊት በምክር ቤቱ አቅጣጫ ተቀምጧል።
ይህንንም እንዲያስፈፅም የኢፌዴሪ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ኃላፊነት እንደተሰጠው ተናግረዋል።
በዚህም የክዋኔ ኦዲት መደረጉን አንስተው፤ በቀጣይ ጊዜያት የፋይናንስ ኦዲት በማከናወን እስከ ግንቦት 15 ድረስ የገንዘብና ንብረት ርክክብ እንዲፈፀም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025