የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ለወሎ ተርሸሪ ኬር የህክምና እና የማስተማሪያ ሆስፒታል ግንባታ የተሰበሰበ ገንዘብና ንብረት እስከ ግንቦት 15 ድረስ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ርክክብ እንዲፈፀም ምክር ቤቱ አቅጣጫ አስቀመጠ

Apr 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ለወሎ ተርሸሪ ኬር የህክምና እና የማስተማሪያ ሆስፒታል ግንባታ የተሰበሰበ ገንዘብና ንብረት የፋይናንስ ኦዲት በማከናወን እስከ ግንቦት 15 ድረስ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ርክክብ እንዲፈፀም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

የወሎ ተርሸሪ ኬርና የማስተማሪያ ሆስፒታል ፕሮጀክት በጎ አድራጎት ኮሚቴ ከወሎ ዩኒቨርሲቲ ጋር ፕሮጀክት ጽህፈት ቤቱን ለመዝጋት የሚደረግ የገንዘብና የንብረት የቅድመ ርክክብ ውይይት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።

በመድረኩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር)፣ የኢፌዴሪ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን ቢራቱ፣ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አወል ስዒድ (ዶ/ር) የወሎ ተርሸሪ ኬር እና የማስተማሪያ የወሎ ሆስፒታል በጎ አድራጎት ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ጣይቱ ዓሊ እና የአከባቢው ማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።

በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ዩኒቨርሲቲው የወሎ ተርሸሪ ኬር የህክምና እና የማስተማሪያ ሆስፒታል ስም የተሰበሰበ ገንዘብ እንዲረከብ ከወራት በፊት በምክር ቤቱ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ይህንንም እንዲያስፈፅም የኢፌዴሪ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ኃላፊነት እንደተሰጠው ተናግረዋል።

በዚህም የክዋኔ ኦዲት መደረጉን አንስተው፤ በቀጣይ ጊዜያት የፋይናንስ ኦዲት በማከናወን እስከ ግንቦት 15 ድረስ የገንዘብና ንብረት ርክክብ እንዲፈፀም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025