የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ለወሎ ተርሸሪ ኬር የህክምና እና የማስተማሪያ ሆስፒታል ግንባታ የተሰበሰበ ገንዘብና ንብረት እስከ ግንቦት 15 ድረስ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ርክክብ እንዲፈፀም ምክር ቤቱ አቅጣጫ አስቀመጠ

Apr 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ለወሎ ተርሸሪ ኬር የህክምና እና የማስተማሪያ ሆስፒታል ግንባታ የተሰበሰበ ገንዘብና ንብረት የፋይናንስ ኦዲት በማከናወን እስከ ግንቦት 15 ድረስ ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ርክክብ እንዲፈፀም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

የወሎ ተርሸሪ ኬርና የማስተማሪያ ሆስፒታል ፕሮጀክት በጎ አድራጎት ኮሚቴ ከወሎ ዩኒቨርሲቲ ጋር ፕሮጀክት ጽህፈት ቤቱን ለመዝጋት የሚደረግ የገንዘብና የንብረት የቅድመ ርክክብ ውይይት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።

በመድረኩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር)፣ የኢፌዴሪ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን ቢራቱ፣ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አወል ስዒድ (ዶ/ር) የወሎ ተርሸሪ ኬር እና የማስተማሪያ የወሎ ሆስፒታል በጎ አድራጎት ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ጣይቱ ዓሊ እና የአከባቢው ማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።

በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ዩኒቨርሲቲው የወሎ ተርሸሪ ኬር የህክምና እና የማስተማሪያ ሆስፒታል ስም የተሰበሰበ ገንዘብ እንዲረከብ ከወራት በፊት በምክር ቤቱ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ይህንንም እንዲያስፈፅም የኢፌዴሪ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ኃላፊነት እንደተሰጠው ተናግረዋል።

በዚህም የክዋኔ ኦዲት መደረጉን አንስተው፤ በቀጣይ ጊዜያት የፋይናንስ ኦዲት በማከናወን እስከ ግንቦት 15 ድረስ የገንዘብና ንብረት ርክክብ እንዲፈፀም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026