አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተውን ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በአውሮፓ ህብረት የውጭ ግንኙነት ቢሮ የኢኮኖሚ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሳይመን ሞርዱ ከተመራ የህብረቱ የከፍተኛ ባለስልጣናት ልዑካ ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ የግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚ ልማት፣ በንግድ እና በኢንቨስትመንት ያለውን ተሳትፎ በማሳደግ የሁለቱን ወገኖች ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።
ምክክሩ ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ትብብራቸውን የጀመሩበት 50ኛ ዓመት እና በቅርቡ ከተፈራረሙት አዲስ ስምምነት ጋር መገናኘቱ ሁለቱ ወገኖች ትብብራቸውን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት እንደሚያመላክት ተገልጿል።
የአውሮፓ ህብረት በመሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ላይ ትኩረቱን ባደረገው "Global Gateway" ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ ተጠቃሚ መሆን በምትችልበት ሁኔታ ላይም ምክክር ተደርጓል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ለልዑኩ ስለ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ማሻሻያው የግሉ ዘርፍ የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እና የኢኮኖሚ ድርሻ ማሳደግ አበይት ትኩረቱን ማድረጉን ገልጸዋል።
ቴሌኮምን ጨምሮ ከዚህ በፊት ለውጭ ኢንቨስትመንት ዝግ የነበሩ ቁልፍ መስኮችን ክፍት ማድረግን ጨምሮ እየተተገበሩ ያሉ ማዕቀፎች የንግድ ስራ ምቹነትና የኢንቨስትመንት ከባቢ አየር ለመፍጠር አስተዋጽኦ ማድረጉን ጠቁመዋል።
የአውሮፓ ህብረት የውጭ ግንኙነት ቢሮ የኢኮኖሚ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሳይመን ሞርዱ ህብረቱ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ትብብር ከልማት ድጋፍ ወደ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረገ አጋርነት ለመቀየር ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በኢንቨስትመንት እና ዘላቂ የስራ እድል ፈጠራ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ አመልክተዋል።
በሌላ በኩል የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረትን የቁጥጥር ደንብን ተከትላ ቡናን ጨምሮ የተለያዩ ምርቶችን ማቅረብ በምትችልባቸው አማራጮች ላይ ድጋፍ እንደሚያደርግም ተናግረዋል።
ሁለቱ ወገኖች ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር መስማማታቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025