
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ):- ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተውን ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በአውሮፓ ህብረት የውጭ ግንኙነት ቢሮ የኢኮኖሚ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሳይመን ሞርዱ ከተመራ የህብረቱ የከፍተኛ ባለስልጣናት ልዑካ ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ የግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚ ልማት፣ በንግድ እና በኢንቨስትመንት ያለውን ተሳትፎ በማሳደግ የሁለቱን ወገኖች ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።
ምክክሩ ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት ትብብራቸውን የጀመሩበት 50ኛ ዓመት እና በቅርቡ ከተፈራረሙት አዲስ ስምምነት ጋር መገናኘቱ ሁለቱ ወገኖች ትብብራቸውን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት እንደሚያመላክት ተገልጿል።
የአውሮፓ ህብረት በመሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ላይ ትኩረቱን ባደረገው "Global Gateway" ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ ተጠቃሚ መሆን በምትችልበት ሁኔታ ላይም ምክክር ተደርጓል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ለልዑኩ ስለ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ማሻሻያው የግሉ ዘርፍ የኢንቨስትመንት ተሳትፎ እና የኢኮኖሚ ድርሻ ማሳደግ አበይት ትኩረቱን ማድረጉን ገልጸዋል።
ቴሌኮምን ጨምሮ ከዚህ በፊት ለውጭ ኢንቨስትመንት ዝግ የነበሩ ቁልፍ መስኮችን ክፍት ማድረግን ጨምሮ እየተተገበሩ ያሉ ማዕቀፎች የንግድ ስራ ምቹነትና የኢንቨስትመንት ከባቢ አየር ለመፍጠር አስተዋጽኦ ማድረጉን ጠቁመዋል።
የአውሮፓ ህብረት የውጭ ግንኙነት ቢሮ የኢኮኖሚ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ምክትል ዋና ጸሐፊ ሳይመን ሞርዱ ህብረቱ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ትብብር ከልማት ድጋፍ ወደ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረገ አጋርነት ለመቀየር ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በኢንቨስትመንት እና ዘላቂ የስራ እድል ፈጠራ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ አመልክተዋል።
በሌላ በኩል የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረትን የቁጥጥር ደንብን ተከትላ ቡናን ጨምሮ የተለያዩ ምርቶችን ማቅረብ በምትችልባቸው አማራጮች ላይ ድጋፍ እንደሚያደርግም ተናግረዋል።
ሁለቱ ወገኖች ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር መስማማታቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026