የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ባለፉት ዘጠኝ ወራት 374 የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎች ወደ ስራ ገብተዋል-ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦በበጀት አመቱ ዘጠኝ ወራት 374 ቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎች ወደ ስራ መግባታቸውን የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።


ንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የ2017 የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እያካሄደ ነው።


መድረኩ ቀጣናዊ ትስስር እና አለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነት ለንግድ ዘርፍ እድገት በሚል መሪ ሀሳብ ነው እየተካሄደ ያለው።


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥የበጀት አመቱ ዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ከእቅድ በላይ የተፈጸመበት ነው።


ምቹ የንግድ ከባቢን ከመፍጠር አኳያ ከፍተኛ ስራ መሰራቱን ተከትሎ በበጀት አመቱ ዘጠኝ ከእቅድ በላይ ውጤት እንዲመዘገብ እንዳስቻለ አንስተዋል።


በነዳጅ ግብይት ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመፍታት የተከናወነው ስራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚህ ቀደም የነበረውም የሲሚንቶ እጥረት መፍታት መቻሉን አንስተዋል።


ከአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና በተያያዘም የታሪፍ ማስማማት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።


ከቅዳሜ እና እሁድ ገበያ አንጻርም ባለፉት ዘጠኝ ወራት 374 ተጨማሪ ገበያዎች ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል።


በጀት አመቱ ዘጠኝ ወራት ከወጭ ንግድ ከ4 ነጥብ 5 ቢልዮን ዶላር በላይ መገኘቱን ጠቅሰው፤በወጭ ንግድ የተገኘው ውጤት በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው መሆኑን አመላክተዋል።


በበጀት አመቱ በተመዘገቡ ውጤቶች በማጠናከር በቀጣይ የላቀ ውጤት ለማምጣት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026