
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦በበጀት አመቱ ዘጠኝ ወራት 374 ቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎች ወደ ስራ መግባታቸውን የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።
ንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የ2017 የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እያካሄደ ነው።
መድረኩ ቀጣናዊ ትስስር እና አለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነት ለንግድ ዘርፍ እድገት በሚል መሪ ሀሳብ ነው እየተካሄደ ያለው።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥የበጀት አመቱ ዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ከእቅድ በላይ የተፈጸመበት ነው።
ምቹ የንግድ ከባቢን ከመፍጠር አኳያ ከፍተኛ ስራ መሰራቱን ተከትሎ በበጀት አመቱ ዘጠኝ ከእቅድ በላይ ውጤት እንዲመዘገብ እንዳስቻለ አንስተዋል።
በነዳጅ ግብይት ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመፍታት የተከናወነው ስራ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚህ ቀደም የነበረውም የሲሚንቶ እጥረት መፍታት መቻሉን አንስተዋል።
ከአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና በተያያዘም የታሪፍ ማስማማት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።
ከቅዳሜ እና እሁድ ገበያ አንጻርም ባለፉት ዘጠኝ ወራት 374 ተጨማሪ ገበያዎች ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል።
በጀት አመቱ ዘጠኝ ወራት ከወጭ ንግድ ከ4 ነጥብ 5 ቢልዮን ዶላር በላይ መገኘቱን ጠቅሰው፤በወጭ ንግድ የተገኘው ውጤት በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው መሆኑን አመላክተዋል።
በበጀት አመቱ በተመዘገቡ ውጤቶች በማጠናከር በቀጣይ የላቀ ውጤት ለማምጣት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025