
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ4ሺህ 254 ኪሎ ግራም በላይ የወርቅ ምርት ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ገለጸ።
ክንውኑ ከዕቅዱ በ2 ሺህ 404 ኪሎ ግራም ብልጫ እንዳለውም ተመላክቷል።
የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጁሉ ጊሎ ለኢዜአ እንደገለጹት እንደ ሀገር የብዝሃ ኢኮኖሚ አውታር ተብለው ተለይተው በልዩ ትኩረት እየተሰራባቸው ከሚገኙ ዘርፎች መካከል አንዱ የማዕድን ልማት መሆኑን ተናግረዋል።
ይህንንም ታሳቢ በማድረግ በክልሉ ያለውን ሰፊ የወርቅ ማዕድን ሀብት ከብክነት በመታደግ ጥቅም ላይ ለማዋል በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ በባህላዊ፣ በልዩ አነስተኛና በወርቅ አምራች ኩባንያዎች ከ4ሺህ 254 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ተመርቶ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን ተናግረዋል።
ለብሔራዊ ባንክ ገቢ የተደረገው የወርቅ ምርት ከእቅዱ በ2ሺህ 254 ኪሎ ግራም ብልጫ ያለው መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
ይህም ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ተግባራዊ በመደረጉና የተሻለ ሰላም በመኖሩ የተገኘ ውጤት መሆኑን ተባግረዋል።
እንዲሁም በቴክኖሎጂ የታገዘ የወርቅ ልማትና ከክልል እስከ ወረዳ የተጠናከረ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በመደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በዘርፉ ከተገኘው ስኬት በተጨማሪ ከስድስት ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል መፈጠሩን ጠቁመዋል።
በቀጣዮቹ ሶስት ወራትም የተጀመሩ ስራዎችን ይበልጥ በማጠናከር ለብሔራዊ ባንክ የሚቀርበውን የወርቅ ምርት ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025