የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ4ሺህ 254 ኪሎ ግራም በላይ የወርቅ ምርት ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል

Apr 11, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ4ሺህ 254 ኪሎ ግራም በላይ የወርቅ ምርት ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ገለጸ።

ክንውኑ ከዕቅዱ በ2 ሺህ 404 ኪሎ ግራም ብልጫ እንዳለውም ተመላክቷል።

የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጁሉ ጊሎ ለኢዜአ እንደገለጹት እንደ ሀገር የብዝሃ ኢኮኖሚ አውታር ተብለው ተለይተው በልዩ ትኩረት እየተሰራባቸው ከሚገኙ ዘርፎች መካከል አንዱ የማዕድን ልማት መሆኑን ተናግረዋል።

ይህንንም ታሳቢ በማድረግ በክልሉ ያለውን ሰፊ የወርቅ ማዕድን ሀብት ከብክነት በመታደግ ጥቅም ላይ ለማዋል በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ በባህላዊ፣ በልዩ አነስተኛና በወርቅ አምራች ኩባንያዎች ከ4ሺህ 254 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ተመርቶ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን ተናግረዋል።

ለብሔራዊ ባንክ ገቢ የተደረገው የወርቅ ምርት ከእቅዱ በ2ሺህ 254 ኪሎ ግራም ብልጫ ያለው መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

ይህም ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ተግባራዊ በመደረጉና የተሻለ ሰላም በመኖሩ የተገኘ ውጤት መሆኑን ተባግረዋል።

እንዲሁም በቴክኖሎጂ የታገዘ የወርቅ ልማትና ከክልል እስከ ወረዳ የተጠናከረ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በመደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት በዘርፉ ከተገኘው ስኬት በተጨማሪ ከስድስት ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል መፈጠሩን ጠቁመዋል።

በቀጣዮቹ ሶስት ወራትም የተጀመሩ ስራዎችን ይበልጥ በማጠናከር ለብሔራዊ ባንክ የሚቀርበውን የወርቅ ምርት ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025