
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ4ሺህ 254 ኪሎ ግራም በላይ የወርቅ ምርት ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ገለጸ።
ክንውኑ ከዕቅዱ በ2 ሺህ 404 ኪሎ ግራም ብልጫ እንዳለውም ተመላክቷል።
የክልሉ ማዕድን ሀብት ልማት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጁሉ ጊሎ ለኢዜአ እንደገለጹት እንደ ሀገር የብዝሃ ኢኮኖሚ አውታር ተብለው ተለይተው በልዩ ትኩረት እየተሰራባቸው ከሚገኙ ዘርፎች መካከል አንዱ የማዕድን ልማት መሆኑን ተናግረዋል።
ይህንንም ታሳቢ በማድረግ በክልሉ ያለውን ሰፊ የወርቅ ማዕድን ሀብት ከብክነት በመታደግ ጥቅም ላይ ለማዋል በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ በባህላዊ፣ በልዩ አነስተኛና በወርቅ አምራች ኩባንያዎች ከ4ሺህ 254 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ተመርቶ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን ተናግረዋል።
ለብሔራዊ ባንክ ገቢ የተደረገው የወርቅ ምርት ከእቅዱ በ2ሺህ 254 ኪሎ ግራም ብልጫ ያለው መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
ይህም ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ተግባራዊ በመደረጉና የተሻለ ሰላም በመኖሩ የተገኘ ውጤት መሆኑን ተባግረዋል።
እንዲሁም በቴክኖሎጂ የታገዘ የወርቅ ልማትና ከክልል እስከ ወረዳ የተጠናከረ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች በመደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በዘርፉ ከተገኘው ስኬት በተጨማሪ ከስድስት ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል መፈጠሩን ጠቁመዋል።
በቀጣዮቹ ሶስት ወራትም የተጀመሩ ስራዎችን ይበልጥ በማጠናከር ለብሔራዊ ባንክ የሚቀርበውን የወርቅ ምርት ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026