አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-የትራንስፖርት ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የጭነት ትራንስፖርትን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር የሚያስችል የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) ሲስተም አስጀመረ።
የትራንስፖርትና ሎጅስቲክ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ሲስተሙን መርቀው አስጀምረዋል።
በምረቃ ስነስርዓቱ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የትራንስፖርትና መሰረተ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታለፍ ፍትህዓወቅ፣የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጊ ቦሩ እና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) በኢትዮጵያ የጭነት ትራንስፖርት ለመቆጣጠር እና ለማስተዳደር የተዘጋጀ ሁሉን አቀፍ ዲጂታል ስርዓት መሆኑም ተገልጿል።
ሲስተሙ የተቀናጀና የተቀላጠፈ የሎጅስቲክስ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችልም ተመላክቷል።
ከዚህም በተጨማሪ ዘርፉን የሚያዘምን ከመሆኑ በተጨማሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግርን በመቅረፍ የህዝብን እርካታ የሚያሳድግ መሆኑ ተገልጿል።
ሲስተሙ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በተለያየ ዘርፍ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል አንዱ መሆኑም እንዲሁ።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025