
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-የትራንስፖርት ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የጭነት ትራንስፖርትን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር የሚያስችል የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) ሲስተም አስጀመረ።
የትራንስፖርትና ሎጅስቲክ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ሲስተሙን መርቀው አስጀምረዋል።
በምረቃ ስነስርዓቱ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የትራንስፖርትና መሰረተ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታለፍ ፍትህዓወቅ፣የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጊ ቦሩ እና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) በኢትዮጵያ የጭነት ትራንስፖርት ለመቆጣጠር እና ለማስተዳደር የተዘጋጀ ሁሉን አቀፍ ዲጂታል ስርዓት መሆኑም ተገልጿል።
ሲስተሙ የተቀናጀና የተቀላጠፈ የሎጅስቲክስ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችልም ተመላክቷል።
ከዚህም በተጨማሪ ዘርፉን የሚያዘምን ከመሆኑ በተጨማሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግርን በመቅረፍ የህዝብን እርካታ የሚያሳድግ መሆኑ ተገልጿል።
ሲስተሙ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በተለያየ ዘርፍ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል አንዱ መሆኑም እንዲሁ።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026