የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የተቀናጀ የጭነት ትራንስፖርት አስተዳደር ስርዓትን አስጀመረ

Apr 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-የትራንስፖርት ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የጭነት ትራንስፖርትን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር የሚያስችል የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) ሲስተም አስጀመረ።


የትራንስፖርትና ሎጅስቲክ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ሲስተሙን መርቀው አስጀምረዋል።


በምረቃ ስነስርዓቱ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የትራንስፖርትና መሰረተ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታለፍ ፍትህዓወቅ፣የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጊ ቦሩ እና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።


የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) በኢትዮጵያ የጭነት ትራንስፖርት ለመቆጣጠር እና ለማስተዳደር የተዘጋጀ ሁሉን አቀፍ ዲጂታል ስርዓት መሆኑም ተገልጿል።


ሲስተሙ የተቀናጀና የተቀላጠፈ የሎጅስቲክስ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችልም ተመላክቷል።


ከዚህም በተጨማሪ ዘርፉን የሚያዘምን ከመሆኑ በተጨማሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግርን በመቅረፍ የህዝብን እርካታ የሚያሳድግ መሆኑ ተገልጿል።


ሲስተሙ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በተለያየ ዘርፍ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል አንዱ መሆኑም እንዲሁ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025