
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-የትራንስፖርት ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የጭነት ትራንስፖርትን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር የሚያስችል የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) ሲስተም አስጀመረ።
የትራንስፖርትና ሎጅስቲክ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ሲስተሙን መርቀው አስጀምረዋል።
በምረቃ ስነስርዓቱ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የትራንስፖርትና መሰረተ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ታለፍ ፍትህዓወቅ፣የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጊ ቦሩ እና ሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) በኢትዮጵያ የጭነት ትራንስፖርት ለመቆጣጠር እና ለማስተዳደር የተዘጋጀ ሁሉን አቀፍ ዲጂታል ስርዓት መሆኑም ተገልጿል።
ሲስተሙ የተቀናጀና የተቀላጠፈ የሎጅስቲክስ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችልም ተመላክቷል።
ከዚህም በተጨማሪ ዘርፉን የሚያዘምን ከመሆኑ በተጨማሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግርን በመቅረፍ የህዝብን እርካታ የሚያሳድግ መሆኑ ተገልጿል።
ሲስተሙ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በተለያየ ዘርፍ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል አንዱ መሆኑም እንዲሁ።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025