መቀሌ፤ሚያዚያ 2/2017(ኢዜአ)፦በትግራይ ክልል ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲነቃቃና መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ እንዲሆን በትኩረት ይሰራል ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ገለጹ።
መጋቢት 30/2017 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሬዚዳንትነት ርክክብ ሥነ-ሥርዓት መካሄዱ ይታወቃል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በሥነ-ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የትግራይ ህዝብ ሰላምና መረጋጋት አግኝቶ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን መንግስት የተጠናከረ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት ሆነው የተሾሙት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ፥ በቀጣይ ወራት ለማከናወን ያቀዷቸውን ሥራዎች አስመልክተው ዛሬ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።
ሌተናል ጀነራል ታደሰ ከካቢኔያቸው ጋር ዛሬ ስብሰባ በማካሄድ በቀጣዩ ወራት ሊከናወኑ የሚገባቸው ሥራዎች ላይ መክረዋል።
በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት ላይ እያንዳንዱ የመንግስት ተቋማት እቅዱን እንዲከልስና የቀጣይ በጀት ዓመት እቅድ እንዲያዘጋጅ አሳስበዋል።
የሁሉም ሥራዎች ማዕከል የሆነው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተሟላ መንገድ ተግባራዊ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል።
የትግራይ ህዝብ ሰላምና ደህንነት እንዲጠበቅ፤ የክልሉ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲነቃቃ የሚያደርግና መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ውጤት የሚያመጣ ስራ ይሰራል ነው ያሉት።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025