
መቀሌ፤ሚያዚያ 2/2017(ኢዜአ)፦በትግራይ ክልል ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲነቃቃና መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ እንዲሆን በትኩረት ይሰራል ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ገለጹ።
መጋቢት 30/2017 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሬዚዳንትነት ርክክብ ሥነ-ሥርዓት መካሄዱ ይታወቃል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በሥነ-ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የትግራይ ህዝብ ሰላምና መረጋጋት አግኝቶ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን መንግስት የተጠናከረ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት ሆነው የተሾሙት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ፥ በቀጣይ ወራት ለማከናወን ያቀዷቸውን ሥራዎች አስመልክተው ዛሬ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።
ሌተናል ጀነራል ታደሰ ከካቢኔያቸው ጋር ዛሬ ስብሰባ በማካሄድ በቀጣዩ ወራት ሊከናወኑ የሚገባቸው ሥራዎች ላይ መክረዋል።
በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት ላይ እያንዳንዱ የመንግስት ተቋማት እቅዱን እንዲከልስና የቀጣይ በጀት ዓመት እቅድ እንዲያዘጋጅ አሳስበዋል።
የሁሉም ሥራዎች ማዕከል የሆነው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተሟላ መንገድ ተግባራዊ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል።
የትግራይ ህዝብ ሰላምና ደህንነት እንዲጠበቅ፤ የክልሉ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲነቃቃ የሚያደርግና መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ውጤት የሚያመጣ ስራ ይሰራል ነው ያሉት።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026