የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ኢኮኖሚው እንዲነቃቃና መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ እንዲሆን በትኩረት ይሰራል - ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ

Apr 11, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ሚያዚያ 2/2017(ኢዜአ)፦በትግራይ ክልል ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲነቃቃና መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ እንዲሆን በትኩረት ይሰራል ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ገለጹ።


መጋቢት 30/2017 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሬዚዳንትነት ርክክብ ሥነ-ሥርዓት መካሄዱ ይታወቃል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በሥነ-ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የትግራይ ህዝብ ሰላምና መረጋጋት አግኝቶ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን መንግስት የተጠናከረ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።


የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት ሆነው የተሾሙት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ፥ በቀጣይ ወራት ለማከናወን ያቀዷቸውን ሥራዎች አስመልክተው ዛሬ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።


ሌተናል ጀነራል ታደሰ ከካቢኔያቸው ጋር ዛሬ ስብሰባ በማካሄድ በቀጣዩ ወራት ሊከናወኑ የሚገባቸው ሥራዎች ላይ መክረዋል።


በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት ላይ እያንዳንዱ የመንግስት ተቋማት እቅዱን እንዲከልስና የቀጣይ በጀት ዓመት እቅድ እንዲያዘጋጅ አሳስበዋል።


የሁሉም ሥራዎች ማዕከል የሆነው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተሟላ መንገድ ተግባራዊ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል።


የትግራይ ህዝብ ሰላምና ደህንነት እንዲጠበቅ፤ የክልሉ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲነቃቃ የሚያደርግና መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ውጤት የሚያመጣ ስራ ይሰራል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026