የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ኢኮኖሚው እንዲነቃቃና መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ እንዲሆን በትኩረት ይሰራል - ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ

Apr 11, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ሚያዚያ 2/2017(ኢዜአ)፦በትግራይ ክልል ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲነቃቃና መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ እንዲሆን በትኩረት ይሰራል ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ገለጹ።


መጋቢት 30/2017 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሬዚዳንትነት ርክክብ ሥነ-ሥርዓት መካሄዱ ይታወቃል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ በሥነ-ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የትግራይ ህዝብ ሰላምና መረጋጋት አግኝቶ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን መንግስት የተጠናከረ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።


የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት ሆነው የተሾሙት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ፥ በቀጣይ ወራት ለማከናወን ያቀዷቸውን ሥራዎች አስመልክተው ዛሬ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።


ሌተናል ጀነራል ታደሰ ከካቢኔያቸው ጋር ዛሬ ስብሰባ በማካሄድ በቀጣዩ ወራት ሊከናወኑ የሚገባቸው ሥራዎች ላይ መክረዋል።


በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት ላይ እያንዳንዱ የመንግስት ተቋማት እቅዱን እንዲከልስና የቀጣይ በጀት ዓመት እቅድ እንዲያዘጋጅ አሳስበዋል።


የሁሉም ሥራዎች ማዕከል የሆነው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተሟላ መንገድ ተግባራዊ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል።


የትግራይ ህዝብ ሰላምና ደህንነት እንዲጠበቅ፤ የክልሉ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲነቃቃ የሚያደርግና መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ውጤት የሚያመጣ ስራ ይሰራል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025